የበረከት መሸታ ቤት።

         የበረከት መሸታ ቤት በቸረቸራ፤ ሴራ በገጀራ።

 „የሰማነው ነገር ሁሉ ማስቀረት አይችልምና የቀሊል ሰው ልቦና እንደ ሰባራ መዳጋ ነው።“ (ምዕራፍ  ፳፩ ቁጥር ፲፬)
                     ከሥርጉተ ሥላሴ 07.03.2018 (ከገዳማዊዋ ሐገር ከሲዊዚዬ።)
  • ·         ራጫ ጨለማ።

በጽሞና ቢሰላ፤ ከልብ ተሁኖ ቢደመጥ የአሁኑ የግራጫ ጨላማ አልጋወራሽ የሆኑት አቶ በረከት ስምዖን ያሰሉት መንገድ እኮ  የኢትዮጵያን ማንነት እጅግ ረግረግ ላይ የሚከት የቁርሾ አባዜ ነው። አቶ ደመቀ መኮነን ሆኑ ዶር. ገብረጽዮን ገብረሚኬኤል በስጋ ፈቃድ እጅግ የረከሰ ሰብዕና ያላቸው ናቸው። በሌላ በኩል  አቶ ሽፈራው ሽጉጤን አክሎ ዶር ገብረጽዮን ገብረሚኬአል በአማራ ዘር ጥፋት ተከሳሽ ሲሆኑ ቀን የሚጠብቅ የወንጀል የህሊና እስረኛ ናቸው። ደመነፍሳቸው ነው የሚወዛወዘው። ዕድሉን አግኝተው ውጪ ከዓለምአቀፉ ማህበረሰብ ጋር የመሰብሰብ ሁኔታ ቢገጥማቸው የመሳቂያ መደበር ብቻ ሳይሆን የተኮፈሱበት ፉኛ ይፈነዳል። 

ምን አለን ብለው ይሆን ለዚህ ቦታ የሚሰናዱት፤ ከሰብዕና ሰብና፤ ከብቃት ብቃት የሌላቸው ራሳቸውን ለመግለጽ አንዲት ቃል ሊደመጥላቸው የማይችሉ ኳካቴዎች እንዲህ 4 ኪሎ ላይ ገበርዲን አይችለው የለ ሥጋን፤ ከረባት አይችለው የለ ጥንዝልን ተሸከሞ ለጉድነቱ በገመና ድውለት መሰናዳቱ ውልቅልቅ የሚያወጣ ስለመሆኑ ያሰቡበት አይመስልም። ልብስ እኮ ገመናን ቢሸፍን እንጂ ፈተናን አያሳልፍም፤ ነፍስ ካለ መነገዳገድ አይቀርም ሆኖ ነው እንጂ ሸሽጉኝ ደብቁኝ የሚያሰኝ ጉድ ተሸክሞ አደባባይ ላይ መሰለፍ መካሪ የለንም ያሰኛል? ሐገር መምራት እኮ ቃታ መሳብ ሳይሆን ህሊናን መሰራት ነው። ከሌለ ደግሞ ያልነበረው በ አንድ ቀን አይፈጠር። ጸጋም የሚባል አለ። ይህም ብን ብሎ የደረቀ ነው። ከ እክሌ እክሌ ለማለት እንኳን ህሊና ያስፈነጥረዋል። ረግረግ። 
የመሸታ ቤት ባለመሰናዶ እጩዎች።

ኢትዮጵያ ከምትታወቅባቸው የመንነት መለያዎች ሁሉ እጅግ የከበረ ነው ይሄ በሥጋ ፈቃድ ጸያፍ ነገሮች ጋር የንኪኪ ጉዳዮች። በማንኛውም ሁኔታ እኔ የማውቃቸው የትግራይ ልጆች እንዲህ ዓይነት የማገጠ ሰብዕና አይቼባቸውም አላውቅም። እንዲያውም ወግ ማጥበቁን ያበዙታል ነው የሚባለው። 

ሌብነት፤ ወረራ፤ ዘረፋ፤ ውሸት አሁን ደግሞ ግብረ ሰዶም የትግራይ መግለጫ መሆኑ በራሱ እንደ ኢትዮጵያዊ ያሳዝነኛል። እኔ ሲሰርቁም፤ ሲወሩም አላውቃቸውም። በማተባቸው ሲቆሙ፤ ጸያፍ ነገሮችን ሲጸዬፉ ነው የማውቃቸው። እርግጥ ነው ሦስት ሆነን ስንጫወት አራተኛ የትግራይ ልጅ ከመጣች አብራን ስትጫወት የነበረቸው ከነመፈጣራችን ትረሳናለች። ይህን እኔ አሊ የማልለው ተደጋግሞ ያዬሁት ነገር ነው።

ከላይ በጠቀስኳቸው ሰብዕናን የሚለንቁጥ፤ ዕትብትን የሚያዋርድ ባህሪ ገጥሞኝ አይደለም ወያኔ ስልጣን ከመያዙ በፊት ሰምቼ አላውቅም። እኔ በልጅነት ይሄ የሴት እና የወንድ ጓደኛ በሚባል ጉዳይ የማውቃት የትግራይ ልጅ ጓደኛ አልነበረችኝም በፍጹም። ወጣት ወንድሞች ነበሩኝ። ከወንድማዊነት ውጪ በዚህ ዝንባሌ ያዬሁት አንድም ጓደኛ አልነበረኝም። እንግዳ ኪሮስ የሚባሉ የጋራ ጓደኞቻችን ነበሩ። አሁን ይሄ የነነዌ መከራ ስለምን ሙያ ተሁኖ እንደተያዘ አላውቅም።

ዕውነትም የወያኔ ሃርነት ትግራይ ማንፌስቶ መንፈስ የሚመራው የዲያቢሎስ ነው። አሁን ይሄ ገመና ደግሞ አደባባይ ለዓለም ሚዲያ ይቅረብ እዬተባለ ነው። እዛው ትግራይ ላይ ከትሞ ሸጉጡኝ ማለት ሲገባ የግሎባል ሚዲያ ሲሳይ ገመና ወጥቶ ኢትዮጵያ አንገቷን እንድትደፋ፤ ቅስሟ እንዲሰበር፤ እንድታፍርበት ተግተው እዬሰሩ ነው ሰላዩ አቶ በረከት ስምዖን።
ትርፋቸው ኢትዮጵያዊነትን ገናናነት በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ማሸማቀቅ፤ ማቅ ማልበስ፤ አፈር ማስጋጥ ነው። ይሄ እንደ ዜጋ ውስጥን፤ ክብርን የሚመረምር እና የሚፈትን ነው። ማህጸንንም በሃዘን ይፈልጣል። ስሜትን ይሰብራል። አቶ ደመቀ መኮነን ታዳጊ ወጣት አስገድደው ደፈረው ከዛው ገመናቸው ጋር ከትመዋል። አሁን ደግሞ እሳቸው እድሉ ባይሳካላቸው ሌላ መሰል ደግሞ ተተኪ ተዘጋጅቶላቸዋል። መሸታ ቤቱ እስከ አልጋው እስከ አንጣፊው፤ እስከ ባልኮኒው፤ እስከ ዋንጫው 4 ኪሎ ላይ አና ሊል ነው። ውርዴት።

እራሱ በዚህ መንፈስ ውስጥ ኢትዮጵያ ስትታሰብ ይቀፋል፤ ያንገሸግሻል፤ ምጥ ያስይዛል። አዎን ጥሪው የግራጫው ጨለማ ተልዕኮ ለዚህ ነው። ኢትዮጵያን ምልምሎ ድራሿን ማጥፋት። ገዳይነቱ፤ ፋሽትነቱ  አቅዶ እዬከወነው ነው። ይህን አረንቋዊ መከራ ተሸከሚ ተብላለች ዛሬ ደግሞ ኢትዮጵያ። የገማናው ክርፋት አፍሪካን እንደ አህጉርም ያጥነገንጋል - ነገ። የጥቁር ተምሳሌትም ስለሆነች በ ዓለም ዙሪያ ትምክህት ያላቸውን ወገኖቻችን ሁሉ መንፈስ እንኩቶ ያደርጋል። ውርዴ።
በማስተዋል ሆኖ ማድመጥን ለፈቀደ ኢትዮጵያዊነት „ምነው ፈጣሪ ኢትዮጵያን ረሳሃት“ አሰኛል። ከ አንዱ ገዳይ ወደ ሌላ፤ ከ አንዱ ጸያፍ ሴሰኛ ወደ ሌላ። ሌትና ቀን ኢንተርኔት ላይ የሥጋ ፈቃድ ኪወስኮችን ሲያንኳ ውሎ የሚያድረውውየዶር ደብረጽዮን መንፈስ በዬሄደበት ሁሉ የሥጋ ገብያ ሲቃርም ወርዴቱ የእሳቸው ብቻ ሳይሆን የሀገርም፤ የታሪክም ነው። የቅርስም የውርሰም ነው።የገመናው ጥንባት አያስቀርብም ይገፈትራል። እንዲህ ባለ እጅግ በወረደ ሰብዕና የዛገጠ ታሪክ ይዞ በዓለም አደባባይ ሲወጣ ለዛውም የ ኢትዮጵያ ውክል አካል ሆኖ ምነው ባልተፈጠርኩ ያሰኛል። ረመጡ ያርመጠምጣል።
ይህን እጅግ የወረደ ከ እንሳሳም ያነሰ ሰብዕና አሽኮኮ ተደርጎ የ አደባባይ ሰው ለመሆን ማሰቡ በራሱ ግብዝነት ነው። ይህ የውርዴት አረንቋ የሚአሸማቅቅ እንጂ የሚያኮራ ሊሆን አይገባውም። የሚሰቀጥጥ እንጂ ጎሽ የሚአስኝ ሊሆን አይችልም። ከሁሉም የሥነ ምግባር አይነት ከ እነሳሳ ያልተለዬ ሰብዕና እንኳንስ ለሀገር መሪነት ለጉርብትናም ይቀፋል።
አቅም።

አቶ ደመቀ መኮነን የ ኢህአድግ መግለጫ ተብሎ ስሰዬሙ በቃ እኔ እንደ ሐውልት ነበር ያዬሆዋቸው። ምኑ ይደመጣል። ድርቆሽ የሆነ ጉድ። ሰንክሳር የሆነ ጣፊያ። አዬ ያቺ ያልታደለች ሐገር እንዴት እና እንዴት ሆና ይሆን ይሄ ሁሉ ዘመን የተሻገረቸው። ይህ የተሰለለ የ አቅም ኪሳራ ተሸክሞ ጠ/ሚር ደረጃ ውድድር? ለዛውም ዛሬ? እራስ እግሩ ቋያ በሆነበት ስንት የዘመናት ፈተናዎች አፍጠው በመጡበት ወቅት። ቅል ተሸክሞ ቅል ለማምረት ይሆን አይታወቅም?

ወደ ዶር ደብረጽዮን ገብረ ሚኬኤል ዞር ሲባል ሥም አይችለው የለ ያሰኛል። እኔ እሳቸውን ሳይ ትዝ የሚለኝ የ አቶ ሞላ አስገዶም ቃለ ምልልስ ነው። „ደግመን አናያቸውም፤ በሚዲያ መስኮት አይመቷትም“ ብዬም ነበር። ኦወን ከስመው ቀሩ። ዶር ደብረጽዮን ገብረሚኬኤል ሳያቸው ሁለመናቸው፤ ልኬታች ሰብዕናቸው የውስጥ አቅማቸው ሁሉ ከ አቶ ሞላ አስገዶም አንዲት ስንዝር ሊራመድልኝ አልቻለም። የፋደሰ ጉድ። የሚናገሩት እግርና እግሩ እዬተማታ እዛው እፊታቸው ላይ አፈር ሲግጥ ማዬት ይችላሉ። ውልቅልቅ አለ ጉድ። እኔ ሄሮድስ መለስ ዜናዊ የወሰዱት እርምጃ እራሱ ሲበዛባቸው ነው። ለወረዳም እእ ነው። ምን አላቸው ግርማ ሞገሱ አጠረ ቀሊል እኮ ናቸው። የለም ነፍሱ የበነነነ ጉድ ነው ። ሰው ትንሽ ንፋሹን ዋጥ አድርጎ ደመነፍሱን ገርቶ አንዲት የተያያዘች የምትደመጥ ነገር እንዴት መናገር ያቅተዋል፤ ደማቸው ሲፈላ ብቻ ወላፈኑ ይታያል። ለዚህ ቦታ ቀድሞውን ነገር አልተፈጠሩም። ምናቸውም የመሪነት ሰብዕና የላቸውም። አጭርም ቢኮን፤ ቀጭንም ቢኮን የመሪት ግርማ ሞስ አለ። እነዲያውም ብዙ ታዋቂ ሰዎች አጭር እና ቀጫጫ ናቸው አሁን ግራማዊ ቀዳማዊ ሃይለስላሴ አጭርና ቀጫጫ ናቸው፤ ግን ግርማቸው ሞገሳቸው ከሰውነታቸው በላይ ግዙፍ እና ተፈሪ ነው። የ እኒህ እኮ ለ እኔ ቢጤ ተራ ወንበርም በፍጹም ሁኔታ ቅብዕ የሌለው ክው ብሎ የደረቀ ፍለስ የሆነ አመዳም ነገር ነው … አልተሰጣቸውም። መሪ ለመሆን መሪ  ሊያደርግ የሚችል ተፈጥሯዊ ንጥረ ነገር መኖር አለበት። አቅላቸውም መንፈሳቸውም የተላጠ ነው ወይንም የተጋጋጠ። ፍርጃ። ማፈሪያ።
  • ባለገጀራው የጠ/ሚር እጩ፤

ሌላው የሰብዕ ፍጡር አንጡራ ጠላት የሆኑት፤ በጥላቻ መንፈስ የሰመጡት አቶ ሽፈራው ሽጉጤም ቢሆኑ በወንጀለኝነት የሚጠዬቁበት ሁኔታ ጊዜ ቢጠበቅለትም፤ ቢያንስ ወንጀለኛን ለዚህ ታላቅ ቦታ ማጨት ከንቀት በላይ ነው። ለነገሩ ኢትዮጵያ እኮ ለቅጣቷ፡ነው እንዲህ ያለ የመከራ ዘመን ትገፋ ዘንድ ወያኔ ሃርነት ትግራይ የሚባል ጨፋጭፊ እና ዘራፊ የተፈጠረባት፤ በረከት ስምዖን የሚባል የሴራ ቸረቸራ የተጫነባት። ከቶ አቶ በረከት ስምዖን ቢያልፉ መቃብሩ በተለመደው ወይንስ ሬሳቸውን በታሪክ እንደሰማናው እንጦረጦስ ሲወርድ ይታይ ይሆን? የጎነደር የመከራ ቀንበር የዕልቂትና የውርዴት አስፈጻሚው መቼም በተለመደው አኳሆን ቀብራቸው አይጠናቀቅም? አንድ ታምር አርባረቱ ይፈጥር ይሆናል።

ከእንግዲህ ግን ገጀራው ለአማራ ብቻ አይሆንም። ኦሮሞም የተሰላለት ሴራ ይኖራል። ባለፈውም አይተናል ሰምተናል። በ600፣000 ወገኖቻችን የደረሰው የመፈናቀል ሰቆቃው፤ መቼስ ሞቱን ስለለመድነው እንጂ 600 ወጥተው የቀሩት የሬቻ ሰምዕታትም አሉ። አሁን ግን ከዛም የከፋ በተለየየ ስልትና የትዕዛዝ የሚከወን ተመስጥሮ የተያዘ አዲሱ የኤርትራ ማንፌስቶ አይማረኝ ላልምርህ ይሆናል። ኤርትራ ለ አንዲትም ሰከንድ ለ ኦህዲድ ወጣት የለወጥ መብራቶች ከሴራ ትታቀባላች ተብሎ አይታሰብም። ለዚህም አጋፋሪዎች በተጠነቀቅ እዬተጠባበቁ ነው። ኦህዲድ በማንኛውም ሰ ዓትና ሁኔታ የቀጥታም ባይሆን በምግብ ብክለት ከሚደርስው ማንኛውም ትቃት ራሱን መጠበቅ ይነርበታል። መዘናጋት በፍጹም የሌበትም። አሁን ኦህዲድ የሳላ የጥቃት ዘመቻ ይከፈትበታል።

አሁን የሚዶለተው ሁሉ ይሄው ነው። እንዲህ ኢትዮጵያ የልቤ የምትለው የብሄራዊ ጀግና የ አጥቢያ ኮከብ ካኦሮምያ ይወጣል ብላ አልማውም አታውቅም እትዬ ኤርትራ። ናዳ ነው ለገደል ማሚቶ ህልመኛው ለ ኤርትራ መንግሥት ካቢኔ። ቢሆን ወድቃ ካልሆነም የ እርስ በርስ የበቀል ማወራራጃ መሳቂያና መዳለቂያ እንድትሆን ነበር ምኞቱ። ወይ ደግሞ በ እሱ ኮማንድ ፖስት ሥር፤ የጦር አዝማችነት የጸጥታ አስከባሪነት፤ የሰላም ተልዕኮ አጋፋሪነት ባለቀይ ምንጣፍ እሆናለሁ ሲል ኦህዲድ ወሽመጡን ቆረጠው። ወገቡ ከሁለት ተከፈለ። ስለዚህ ከቆዳ መልስ መስሎ የተቀላቀለውን ሰላዩን ያላ የሌለ ሃይሉን ተጠቅሞ ድፍርስ ያለች ኢትዮጵያ ትፈጠር ዘንድ ተግቶ እዬሠራበት ነው። የህዝቡ ብስጭት ጎልቶ እንድ ነገር ቢፈጠር የቆሼው ህልም ዓለማ መታ ነበር። እሳት ነው የሚጠብቀው የ ኤርትራ መንግስት በብጥብጡ ገላጋይ ሆኖ የቅኝ ግዛት ለማድረግ። በ ኢትዮጵውያን ደም እና አጥንት የ ኤርትራ የህልም እንጀራ ሊጎዘጎዝ ቋምጣል። ለዚህም ነው የልሆኑ መጠራቀቅኦችን በማምጣት መንገድ ከፋች የሆኑ በሮች ክርችም ብለው እንዲዘጉ ግራ እዬመከሩ ግራ መንገድ እንዲመርጥ በ አማላጅነት እዬኳተኑ ያሉት ግራጫው ጨላማ አቶ በረከት ስምዖን።
  • ምን ይደርግ።

ወያኔ ሃርነት ትግራይ ከሳጥኑ ወጥቶ አይኑን ከፍቶ ያለቸውን እንጥፍጣፊ እድል መጠቀም ይነርበታል። ለራሱ ቢል፤ እሳት ሲነድ የሚመርጣው የለም። አሁን ያለው ጠበንጃ ጠባቂ መሆኑ ቀርቶ ራሱን ነጻ የሚያወጣ የነፃነት አርበኛ ነው የሚሆነው። ከራስ በላይ ነፈስ የለም እና። ወስጡም የጤሰ ነው። አድሎ፤ ግለት፤ ባይተወርነት፤ ጼአፉ ስድም፤ ስነቱ ተዘርዝሮ አልቃል። ያ ሁሉ ሂሳብ መወራራጃው አጭር ይሆናል።

ቂም አረገዘው አየርም እንደ ሰለማዊው ሽግግር ሩህሩህ አይሆንም። በፍጹም። የተገፋ ህዝብ ሲገነፍል ህግ አይሰራም። ስለዚህም ለራሱ ለወያኔ ሃርነት ትግራይ ይህቺ ወቅት ሳትዘገይ ሳታመልጥም ለሚሊዮኖች ለራሱ ደሞች ሲል፤ ለነገም ለሚፈጠሩትም ካለ እዳቸው ዕዳ ተሻካሚ ስለሚሆኑት የትውልድ አባልተኞችም ሲል በክብር ውርዴትን ቀድሞ ለባለ አቅሙ ከላምንም ግርግር ማስረከብ ይነርበታል። እንደ አቅሙና እንደ ወርዱ በተገባው መጠን ልክ ለመኖርም መወሰን ይነርበታል። ቀኑ አልቋል። አንዲት ነፍስ ሃብት የለውም። ትላቸው እራሱ መርዛም ነው። ምክንያቱም የተገፋው ዘመን ለመግለጽ ቃል የለም። ማጣት ይነራል ብዙ ነገር፤ ግን ትውልድ ማትረፍ ከትርፍ በላይ ነው። አቶ ለማ መግርሳ እኮ አቅማቸው ቢቀር ግርማቸው፤ ለዛቸው ርህርህናቸው የውስጥ ጸትታቸው አንድ ትውልድ ይገነባል፤ ግን ያደረጉት ነገር እግዚአበሄር ወርዶ የማዬት ያህል ነው። 

ከዚህ በላይ ታላቅ ተቋም ሊዘህ ተውልድ ለራሱ ለወያኔም የለውም። ሊነረውም አይችልም። ስለዚህ ጊዜና ቦታ ወሳኝ ነገሮች ናቸው ያማለጠ ይፈሳል የፈሰሰ አይታፈስም። ይሄን ሁሉ በመሳሪያ ተመክቶ ከመወራጨት ይህን የችግር ዘመን በበቀ አዲስ መንፈስና አቅም፤ በጠራ መስምር ሊመራ የሚችል ሙሉ አቅምና ቁመና ላላው አካል ላኦህዲድ መስጠት ግድ ይላል። ደግሞስ የ እናንተው እኮ ነው። እንዲያውም ኢህን ያህል ተቀባይነት ሲአገኝ ደስ ሊል ኩራታችን ተብሎ ሊከበር ይገባል። ኢህድግ እኮ እንደ ኢሰፓ ዘርአልባ መሆን የነበረበት ድርጅት ነው። ምን ነበራችሁ ምንስ መልካም ነገር አላችሁ። በዚህ ዘመን እኮ መለኪያው ተፈጣሯዊነት እና ሰዋዊነት ብቻና ብቻ ነው። ብናኝ ነፍ መጠጋጋት የሚችል አላችሁን? ድርቅ የመታው ድርጅት ተሸክማችሁ ነው ያላችሁት። ደግሞም ፈርሷል። ሃብት የላችሁም የሥነ ልቦና። አቅም የላችሁም የብቃት። እጃችሁን ያወጣው ኦህዲድ ነው። ዕድሜ ላኦህዲድ ብላቸውሁ እንደ ልካችሁ፤ እንደመጠናችሁ ለመኖር መፍቀድ በውዴታ፤ ካልሆነ ግን የሚሆነው አይታወቅም። ከታሪክም፤ ከህዝብ ፍቅርም ሳጥሆኖ እንደባከናችሁ ብን ….

ከህዝብ አገር የወገኑት እንደ ድርጅት ኦህዲድ፤ ብአዴንም በገዱ መንፈስ ውስጥ ያሉ አንበሶች፤ ከ88 አብቼዎች ውስጥ ያሉም ደቡብ ህዝቦች ከኖሩም እንኳን ለዚህ ክብር አበቃችሁ። ይህ ታላቅ ገድል ነው። ያላሰብነው፤ ያላለምነው የመንፈስ ደስታ አጎናጽፋችሁናል። ተጋድላችሁ ባክኖ አይቀርም ኢዘከራል። ሰውን ከማዳን በላይ የቤት  ሥራ የላችሁም እና …
በተረፈ የልብ አድርሱ ኦህዲድ እኔ ነኝ ቀዳሚው ባለታሪክ እያለን ነው። እሰይ አስይ ብለናል እልልም ብለናል። እኛ እናንተ ይህን ድፈሩት እንጂ ቁንጮ ነን ማለታችሁ ያለመነው ነበር። በ እናንተ ውስጥ ደማችን አለ። በ እኛ ውስጥም ደማችሁ አለ። ስለዚህ ሁኑበት ብለናል ኢትዮጵያዊነት እንዲህ አምሮበት ሳዳምጠው ደግሜ በሻማ ብርሃን አጅቤ ነው በርቱልኝ የ እኔ አንበሶች። መንፈሴም ልቦናዬም ለሰከንድ ከ እናንተ ተለይቶ አያውቅም … ክአሰችሁንል። ጊዜ ታሪክ ይሰራል። ታሪክ የሰጣችሁን መሳነዶ አሟልታችሁ መገኘታችሁ ኩራት ሁናች ል። ስንት ረቂቅ ነገሮችን እንደሸፈናችሁ ፈጣሪ ብቻ ነው የሚአውቀው። በዚህ ሂደት ከጎናችሁ ያልተለዬው የአቶ ገዱ መንፈስም የተመሰገነ ይሁን አሜን።
  • የቋያ እሳት ለማህበረ ሽንፍላ።

እንዴት ከተስፋዬ ገበረ ጃርት መንፈስ አምልጠህ መንፈስህን ኢትዮጵያ ላይ ልታሳርፍ ቻልክ? በዬት ሾልከህ ከዚህ ደረስክ? በዬትኛው የስለላ መረብ ሳትታይ ቀርተህ ነው እንዲህ ያመለጥከን? በዬትኛው ጎዳና ተጉዘህ ነው በመላ ኢትዮጵውያን ቅን መንፈስ ባለሙሉ እንደራሴ የሆንከው? አና ብለህ የመንፈስ የሁሉ ጌታ ለመሆንህ የታደልከው እንዴት ተብሎ ነው? ጥርስ ተነክሷል። ይህ ቁጭቱ፤ እልሁ፤ በቀሉ የለማ መንፈስ ተሸናፊ ከሆነ በእጥፍ ድርብ ይቀጥላል። ለዚህም ነው የሴራው መሃንዲስ አቶ ደራጎን ከሸጎሪያቸው ብቅ ብለው የማስጠንቀቂያ መርዛማ ንፋስ ረጫ ረጫ ያደረጉት …. በጀርባቸው በ እጅ አዙር ቅኝ አገዛዝ ህልም ሲባዝኑ የኖሩት የ ኤርተራው ፕ/ ኢሳያስ አፈወርቂም ለ አፍታ የማይዘናጉበት ምህዳር ነው። ሌላ ሥራ የላቸውም ባክነዋል። ፋታ አጥተዋል። ሰላማቸው ታውኳል። ዕድሉ ሊያመልጣቸው ስለሆነ ያለ የሌለ ሃይላቸውን አስተባብረው መርጉን ሊለቁት ተሰናድተዋል። እና ኢትዮጵያ ይህን የመመከት የመንፈስ አቅም ማሰባሰብ ህልሙን ቅዠቱን በቁሙ የማስቀረት ክህሎቱ የላትንም?

ለዚህ ነበር እኮ አማራ ሲታጨድ፤ ሲሳደድ የኖረው። አሁን ያ መንፈስ ሃለ በረከቱን ባፈሰሳባቸው ቅዱሳን ላይ ረበበ ባልተሳበ ቦታ፤ ጊዜ እና ሁኔታ ጎህ ቀደደ። የመንፈስ ልቅናው መሰረት ያያዘ መሆኑ ህሊናዬ ተበላ። ንጹሓ ልብ ተሸለመቸው። እና ማበድ ሲያነስ ነው?  አማራን በይፋ በፖሊሲ ደረጃ ከምድረ ኢትዮጵያ ለማጥፋት የተሴረው ሴራ ምክንያትም እንሆ ለ አደባባይ በቃ። ዘመን አንዲህ ይክሳል። ገብያ የሚሰጠውን የ እናት ልጅ አትሰጠውም የሚሉት ጎነደሬውኦችም ለዚህ ነው።፡
  • የሻብያ ሰላዮች፤

ቀደም ባለው ጊዜ ተሳስቶ እንኳን ቀና ብሎ እንዳይወጣ አሰሳው በበበረከት ኤርትራዊ የስለላ ልዩ ሴል አሉ በሚባሉ ቁልፍ የሃላፊነት ቦታዎች አደናው ሲከወን ነበር። የአማራ ሊሂቃን በስውር እየታደኑ በታክሲ ውስጥ፤ በምግብ ብክልት፤ በአሳቻ ቦታ እየተፈለገ ሲገደሊ ሲሰውሩ ነበር። ሥማቸው ያልታወቀ ባለቤትም የሌላቸው ቤቱ ይቁጠረው። ሌላው ደግሞ ተገፍቶ ይልቀቅልን ተብሎም ውጪ የተላከም ይኖራል፤ ከንፍሮ ጥሬ ያመለጡትም በበረሃ ተንከራተዋል። በተረፈ እዬታደና በነቂስ ባለ ብሩኽ ጭንቅላት አማራ የዓለም አደባባይ የማያውቀው የክንፈ የደህንነት ማስልጠኛ የደህንነት ተቋም ውጦት ቀርቷል። ሥማቸውም አይታወቅም። ህግ ተብዬው፤ ፍ/ቤት ተብዬውም አያውቃቸውም። ይህ የክንፈ የደህንነት ማስልጠኛ ተቋም ታላቁ ተልዕኮው የአማራ ሊሂቅ ማደኛ እና ማክሰሚያ ቦታ ነው - የናዚ ኦሾቲዝም ጉድጓድ።

ሥልጣን ላይ ባለው የወያኔ ሃርነት ትግራይ ሥርዓት፤ የሻብያ ሰላዮች፤ የዛሬው ሳይሆን ቀደመው የኦነግ መንፈስ ማህበርተኞች ሁሉ  በ አማራ ላይ መንፈሳቸው መርግ ነበር። አሁን ማነው ባለተራ ጥመድ ተብሏል ኦሮሞ። የቀደመ፤ ብልህ፤ ብሩህ የሆነ ጭነቅላት ያለው ወጣት የ ኦሮሞ ልጅ የሰሬው ጉድጓድ አቶ በረከት ስምዖን ያሰናዱለትን የመርዝ ፈንጅ ልብ ብሎ አቅሙን ሰብሰብ አድርጎ አቅሙ ላይ ማዋል የግንባር ቀደም ተግባሩ ነው። አሁን ከተቃውሞ ንቅናቄ ትግሉን ወደ ህልውና ማድረግ ይነርበታል - ይመስለኛል። አዬሩ፤ ጠረኑ ሁሉ የሚመች አይደለም።  ብሄሩ ኦሮሞ ብቻ የሆነ ነው እንግዲህ በመብራት የሚፈለገው የሴራኢ ቦንዳ የበረከት ሴል፤ መረብ ሌላ ሃላፊነት እና ተግባር አይነረውም። ለሥራፈቱ ቅራሪ መንፈስም ክፍት የሥራ ቦታ ስለሆነ ደስ ብሎት ይተጋበታል። ስለዚህ፤ ስለዚህ እማ ትንሳኤው መባቻ ላይ በብልህነት በልጦ በመገኘት ስሌት አቀሙን ለ አቅሙ መሸልም ይነርበታል። ካመለጠ ትርፉ መጋጋጥ ብቻ ነው።  በ አማራ የደረሰው የዘር ጥፋት እኮ ሬቻ፤ ጨለንቆ ምልክት ናቸው። አሁን ደግሞ ዕድሉን በረባ ባልረባ የስልት ዕውቅት ማነስ ሃሳቡን ከበተነ ነገ የወዮ ቀን ይሆናል።

ትንሽ አብሾ ለአብሾኛው አቶ በረከት ስምዖን። 
ኢትዮጵያ እንዲህ አማረበት ዘንካታ ሙሉ ወርዳን ተላብሳ መቀነቷን ሸብ አድርጋ፤ በሹሩባዋ ላይም አሰኛትን ጌጥ አክላ፤ ይሄው በ ኦቤኔ ተዘነከትች መንፈሰዎት ድንገት ከሳት የገባ ብላስቲክ እንዳይሆን ውሃ ቢጤ ያዘጋጁ እሺ … ጨምድድድ እንዳይሉ …

ሰበር ዜና - አቶ ለማ መገርሳ አስደንጋጭ ኢህአዴግ ፍራቻ እና ጥላቻ ተቀላቅሎበታል Ethiopia

መሰማት ያለበት ሰበር ዜና። አቶ ለማ መግርሳ ትልቅ እርምጃ ወሰደ።
ኢትዮጲያዊነትን እና አንድነት 20 05 2010

Ethiopia የኦሮሚያ ባለስልጣናት "ሴራ ተሸርቦብናል" አሉ

እኛ ምን እናደርጋለን ሰው እንወዳለን …


አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።