ልጥፎች

ኢትዮጵያዊነት ምንጩና አገነባቡ ከሃሳብ በላይ ነው።

ምስል
ጥፈተኛው ማን ነው? „ከቀና ህግ ወጥተን ሳትን“ መጽሐፈ ጥበብ ምዕራፍ ፭ ቁጥር ፮ ከሥርጉተ © ሥላሴ Sergute © Selassie ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ                                                               መንፈስ! እንዴት ናችሁ የኔዎቹ? ደህና ናችሁ ወይ ? በዛ ሰሞን በአንድ የግል ቪዲዮ እስራኤል አገር አባቶች መደብደባቸውን አዳመጥን አዬንም፤ አሁን ደግሞ ኢትዮጵያ ሻሸመኔ ተመሳሳይ ነገር መፈጸሙን አዬን። የቆዬ ስለመሆኑ አይደለም ጉዳዩ። ጉዟችን ወደዬት ነው? ቀደም ባሉ ጊዜያት ላይ በመ ዶሻ ተቀጥቅጠው ያለፉ ወገኖች አሉን፤ ተገድሎ ተዘቅዝቆ የተሰቀለ ወገንም አለን። መፈናቀሉ፤ መደፈሩ፤ መተዛዘን መመ ከኑም አለ። አጀንዳችንም አይደለም ከሚዲያ ማሟቂያ ባለፈ፤ ሰከን ያለ ተግባር የቸርነት አንበሉ ዮሴፍ ገብሬ ከፈጸመው ውጭ። ያለፈውን ዓመት ትንሳኤን አብሮ ነው ያሳለፈው። ·        ው ጊ ያ ? ይህ የመንፈስ የነፍስ ውጊያ መንስኤው ምንድን ነው? ምን ተማርንበት? ምን አቀድንበት? ምን አጨንበት? ምን አሰብንበት? ምን አስተረቀንበት፤ ምንስ ል ንታረ ቅ አሰብንበት ይህ ነው የዛሬ ጉዳዬ። ·        ምን አሰብ ንበት ስለ ውድቀታችን። ወድቀ ና ል። ወድቀናል ሁላ ች ንም። ስለምን? ትውልዳዊ ድርሻችን ለመወጣት አቅም ስሌለን - የመንፈስ ብርታት መቀኗችን ፈሰስ ስለሚል። በ2008 እንደ አውሮፓውያኑ አቆጣጠር የጸጋዬ ድህረ ገጽን ስጀምር ዋናው ሞቶዬ „ትውልዳዊ ድርሻችን በህብረት እና በ አንድ ነት እንወጣ“ ይል ነበር። ሁለተኛው አጋዥ ሞቶዬ እንደ ቅመም „እልፍ ነን እና እልፍነ ታችን እልፍ እንድርገው“ ይል ነበር።  ለዚህም ለመጀመሪያ

አቤቱታ ለዶር ገዱ አንዳርጋቸው ከቆሰለው ማህጸኔ!

ምስል
ሲከር ይበጠሳል ሲሞላም ይፈሳል! “አቤቱ በድንኳንህ ውስጥ ማን ያድራል? በተቀደሰው ተራራህስ ማን ይኖራል?” መዝሙረ ዳዊት ፲፬ ቁጥር ፩ ይድረስ ለዶር ገዱ አንዳርጋቸው የአማራ ክልላዊ መስተዳደር ፕሬዚዳንት፤ ባህርዳር ·        ጠ ብታ። ጤና ይስጥልኝ ዶር ገዱ አንዳርጋቸው እንዴት ከረሙ? በቅድሚያ በእርስዎ የተመራው ልዑክ ከስሜን አሜሪካ ወደ ባዕት በሰላም ስለገባ ህሊናዬ አርፏል። እኔ የተፈጥሮ አየሩን እራሱ አላምነውምና። መንፈሴ በሰላም ወጥታችሁ ስለመመለሳችሁ ይሰብ እናንተ ደግሞ ስለ ተልዕኳችሁ ሆነ ስኬታችሁ ትጉ፤ እንዲህ ሥራ መከፋፈል … አቨው እና እመው በጸሎት ይርዷችሁ ...  ·        መነ ሻ። https://ethiov.com/single-video/TAoDl6l50Yz የከተሞች መድረክ በወረታ ከተማ ክፍል ሁለት https://www.youtube.com/watch?v=uAhWefWo6V0 የከተሞች መድረክ በወረታ ከተማ ክፍል ሶስት https://www.youtube.com/watch?v=10lqnruXJP8 የከተሞች መድረክ በወረታ ከተማ ክፍል ሶስት ·        የ ቆሰለ ትዝብት ከማህጸን ዕንባ። ትናንት የአማራ የብዙሃን ሚዲያ የወረታ ከተማ ነዋሪዎችን አሰባስቦ ሲያነጋግር የነበረውን ዝግጅት አዳምጥኩኝ። እንዲህ የወለጋ የወ/ሮ ታደሉ መሰል ዕጣ ፈንታ እናቶች ወረታ ላይ እንደሚኖሩ ከገመትኩት በላይ ነው የሆነብኝ። አማራ መሬት ላይ ለ50 ዓመት የሆነውን አውቃለሁኝ። አዲስ አይደለሁም። የወያኔ ሃርነት ትግራይ የማንፌስቶ አስኳል በአማራ መቃብር ላይ ስለምትመሰረተው ታላቋ ትግራይ ህልም ተፈፃሚነት የጦስ ዶሮ አማራ ነው አሁንም አላባራም ...  አማራ ማለቅ