ልጥፎች

ከብርት ፕሬዚዳንት ሳሀለ ወርቅ ዘወዴ ትውፊት ናቸው!

ምስል
መልካምነት ይበጃል። „ወደ ደጋግ ሰዎች የሚላኩ ሪቂቃን የሆኑ መላዕከት ብርሃን ናቸው።“ መጽሐፈ መቃብያ ከልዕ ምዕራፍ ፳ ቁጥር ፲ ከሥርጉተ©ሥላሴ 04.11.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።                       ዋው! የኮ/ ጎሹ ወልዴ ክብር አከበርኩት። ምኞቴም ተሳካ ተመስገን! የጭብጤ መነሻ አሉታዊ ነገሮች አቅም ማግኘት አይገባቸውም ነው። ክፉ ነገር ይወረናል። ክፉ ነገር ይገዛናል። ክፉ ነገር ያሰተዳድረናል - ፈቅደንለት። ቀና በሆኑ ጉዳዮች ላይ እንኳን ስምምነቱ ያን ያህል ነው። ታዲያ በዬት ታልፎ መልካም ነገሮች ሥር ይኑራቸው። ፍሬስ እንዴት ያፈሩ? መልካሞችን መልካም ለማለት ካልተደፈረ፤ መልካም ያልሆኑት መልካም አይደለም ማለት ካልቻልን ታዲያ እኛ ሰው መሆናችን ከምኑ ላይ ነው? እውነት ለመናገር አሉታዊ ነገር ወረራው መልካሞችን እንዳናይ ሸብቦናል። መለዬት አልቻልንም። በጣም ጥሩ የሆኑ መልካም ነገሮች ይታያል ኢትዮጵያ ውስጥ። እጅግ የሚመስጡ ጥሩ ነገሮች አሉ ኢትዮጵያ ውስጥ አሉ፤ አሁን ሴቶችን የፖለቲካ ዕውቅና በመስጠት እረግድ ሉላዊ አብዮት በአብነት እዬተካሄደ ነው ልብ ላለው ልበ ህሊና ብርሃን ላለው፤ እነዚህ አቅም እንዲያገኙ፤ እንዲራቡ፤ እንዲበራከቱ መትጋት ቀርቶ ደግመን ደጋግመን ከክፉ ነገሮች ጋር ልውስውስ አድርገን ግርዶሽ ሰርተን፤ ዝንቅንቅ አድርገን መልካምነትን የተፈጠረበትን ቀን እንዲረግም እናደርገዋለን። ግን ስለምን? የሰው መለያው እኮ ክፉ እና ደጉን የሚለይበት ህሊና ስላለው ነው። ያ ህሊናው እንኳንስ መልካም ነገሮች እያሉ ወደ መልካም ነገር የሚወስዱ ጥሩ ዜናዎች፤ ውጥኖች፤ ጅምሮች፤ ፈሎች፤ ቀንበጥ ሃሳቦች እንኳን ሲኖሩ እነዛ ሃይል ብርታት አግኝተው የመልካም ነገሮች ቤተኛ

የአማራ ተጋድሎ ቀዳሚ ተግባር ለሰላም ዘብ መቆም ነው!

ምስል
የአማራ ተጋድሎ ቀዳሚ ተግባር ለክልሉ ህዝብ ሰላም ዘብ መቆም ነው። „አግዚአብሄርን የሚፈለግ ልብ ደስ ይበለው።“ መጽሐፈ መዋዕል ቀዳማዊ ምዕራፍ ፲፮ ቁጥር ፲ 03.11.2-18 ከሥርጉተ©ሥላሴ ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። አማራ ከዚህ መሪው ጎን መቆም ግድ ይለዋል።  ጦርነት አውዳሚ ነው። ከጦርነት የሚገኝ ትርፍ ቢኖር አመድ እና ቂም በቀል  ብቻ   ነው። ቂም እና በቀል ደግሞ ለቀጣዩ ትውልድ ጸር ነው። ጥቂት ሰዎች  ለውጥ  አልመጣም ይላሉ። በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ በቀና የሚዩት አንዳችም ነገር  አለመኖሩ ሰው ከምን ተሠራ እስከማለት እደርሳለሁኝ። ፍጹምነት ከሰው  መጠበቅ ዓይነት ነው። ግድፈት የለም ማለቴ አይደለም። ግድፈት ራሱ ሰውኛ   እንጂ ሮበትኛ አይደለም። ብቻ ሁሉንም ድፍጥጥ ሲያደርጉት የትኛው  ፕላኔት እንዳሉ ይገርመኛል።  እንደ ሥርጉተ ሥላሴ ግን የአማራ የማንነት የህልውና ተጋድሎ ለውጤት የበቃ ነው  ባይ  ነኝ። ኮሽታ የማያሳማ፤ ዕወጁልኝ የማይል ለውጥ አለ። ቀውስ የለም ማለቴ  ግን አይደለም። የግርግር ሙሽሮች በእጃቸው የሰሩት ቀውስ አለ። ያው ሁሉ  የሥልጣን ጥመኛ አይደለ።  ያ ያው ሁሉ የቤተመንግሥት ቀይ ምንጣፍ ምኞተኛ አይደለምን? የአማራ የማንነት ህልውና ተጋድሎው መሰረታዊ ጥያቄዎች መፈታት ለመቻል  የሥርዓቱ አዋራሪሶች ከሥልጣነ ገብታቸው በስልት ማስነሳት ነበር የመጀመሪያው  ረድፈኛ ተግባር። ይህ በሚደንቅ ሁኔታ ተከናውኗል። ርዕዮቱም ቢሆን ሞራው  ነው ያለው። ይህ ስለተከናወነም በሁለቱ የአገር መሰረት ሃይማኖቶች ተፈጥሮ  የነበረው የ27 ዓመት ስንጥቅ ተገጥሟል። ተቋም ለሚበላው ከኦርቶዶክስ  ተዋህዶ እና ከእስልምና በላይ የሚኖሩት ለገሃድዋ ዓለም