#የእምዩ ሲዊዝ ብሄራዊ ቡድን የአልጀርያን ብሄራዊ ቡድን ሁለት #ለምንም ሸኙ። #ሲዊዝ 2: #አልጀሪያ 0
"አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።

የፊፋው ፕሬዚዳንት በተገኙበት በአውሮፓውያኑ ሰዓት አቆጣጠር ከንጋቱ 11.00
ሰዓት በካናዳዋ አንኮበር ከተማ የተካሄደው ጨዋታ በሲዊዝ #አሸናፊነት በመደበኛ
የጨዋታ ጊዜ ውድድሩ ተጠናቋል።
የአልጀሪያ ቡድን እንደ ጣሊያን ቡድን #ጉልበት ቀመስ ነበር ማለት ልቻል። ሲዊዛውያኑ
በዛሬው ጨዋታ የግል ጥረት እና የወል ጥረት የተዋህዱበት ነበር። አዲስ ተጫዋች ቁጥር 7 በጣም
ቅንነት ያለው ነው። ዕድሎችን በማመቻቸት ረገድ ቅንነቱን አይቻለሁ። ፈጣንም ነው።
የሲዊዝ ቡድን ያሳየው #ጥንካሬ ገርሞኛል። በጣም ለውጥ አላቸው። ስጋቴ የነበረው ጎል ጠባቂው ከቦታው
በጣም #ይርቅ ስለነበር ነበር። እንደ ፈረንሳይ፤ እስፔን ያሉ ቡድኖች እንዲህ ዓይነቱን ዕድል በጣም ይጠቀሙበታል።
ስለዚህም የሲዊዝ ብሄራዊ የእግርኳስ ቲም በር ጠባቂ ብዙም ከጎሉ አካባቢ ባይርቅ ለቀጣዩ ጨዋታ ጥሩ ይመስለኛል።
የአልጀሪያ ብሄራዊ የእግር ኳስ ቲም ጥሩ ተጫውተዋል። ብዙ ሞክረዋል።
ሥርጉተ©ሥላሴ
Sergute©Selassie.
03/07/026.
#ኳሲዝም ይለምልም። አሜን!
አስተያየቶች
አስተያየት ይለጥፉ