#መኖሬ #ካንፓሴ። መኖሬ #ኮንፓሴ።

 

"አቤቱ ንጹህ ልብ ፍጠርልኝ።" አሜን።
 
 
 
የእኔ ውድ የምናፍቅህ ግን የማትገኝ በሥራ አጨናንቄ ፋታ የነሳሁህ #አጤ #ወጣትነት እኮ እንዴት ነህ?
 
ለካስ እንዲህ #የምታምር፤ እንዲህም #የምታጓጓም ነበርክ? ግን #ሳላውቅህ #ሳታውቀኝ #ተላለፍን#አትመለስ ነገር፣ #አትገኝ!
ነገር ወጣቶች ሆይ! ዕድሜያችሁ የሚፈቅደውን ሃይማኖታችሁ፣ ትውፊታችን ባህላችን በሚፈቅደው ልክ የአጤ ወጣትነት ሥጦታ እንደ እኔ እንዳታባክኑት አደራየ ከውስጥ ነው፣ ከልቤ እና ከእውነቴ እግዚአብሄርም በሚያውቀው እንዲህ አምር እንደ ነበር #አላውቅም ነበር።
 
ለካንስ ወጣትነት ውበቱ ዲካ የለሽ እንዲህ ነበር። #ገርሞኛል#የዕውነትም #ደንቆኛል። የፖለቲካ ህይወቴን ብቻ ነው እኔ እማውቀው። ሌላማ በወጣትነት ያለው ፈታ፤ ዘና ያለው የሳቅ እና የሰናይ ጊዜ ከወዴት አባቴ፤ የሚገርመው ዛሬም በዛው መቀጠሌ ነው። 
 
የእምየ ሲዊዝሻ ረቂቅ #መንፈሳዊ #ጭምታዊ ድባብም ባልጠላውም፤ የወጣትነት ጊዜየን ባሳለፍኩበት #ክድን ባለ ህይወት እንዲቀጥልም ተጽዕኖ ያለው ይመስለኛል። በወጣትነት ፖለቲከኝነት ሌላው ቀርቶ የአማኑኤል ሥጦታ የሆነውን የደም ግባት እንኳን #እንዳታስተውሉት ግርዶሽ ይሠራል። 
 
የእኔ ክብሮች ደህና ናችሁን? ኑሩልኝ።
ሥርጉትሻ። 26/08/025

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

የእኔ እማ ልዕልቴ እንዴት ነሽ?

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።