ከሩቅ ይጠራኛል / ግጥም

ከሩቅ ይጠራኛል።
„በውኑ ጥብብ አትጮኽምን?“
ምሳሌ ምዕራፍ ፰ ቁጥር፩

ከሥርጉተ ሥላሴ
02.09.2018
ከገዳማዊቷ ሲወዚዬ።

መምር ይመረኛል፤ ልዋህም ብለው እንብዬው ይለኛል።
ጎምዝዞ ይዞኛል፤ ልፈትነው ስልም አይሆንም ይለኛል።
ደማኖም ታቆኛል፤ ልቀቀኝም ስለው ልሽ - ልሰልቅ እንዲህም ይለኛል።
ይለኛል ይለኛል፤ መንሹን አስልፎ ክንደኛ ብሎኛል።

ተረከዝ ተጎርዶ ራመድ ክዶኛል፤
መክዳቱ ክዳቱ ክዳኑ ጥፎኛል።

በትርፈኛ ዘይቤ ዜማ ቀንጥኛል፤
ፈር ተገብ ስለሆንኩ ዓይነት ቀንቦኛል።

ይሆናል አይሆንም „አይም“ ያምርብኛል
„እሺ“ ቢቀርበት እንቆቆ ልኮል።

ለእሷ ከሆነማ፤ ንጋትና ዕውነት ከሩቅ ይጠረኛል
ለሚዛንም ቀኑ ናፍቆቱ ይዞኛል፤

ሸው እንዲያው ሽው እሱን ያሰኘኛል
የእኩልነት ማት ሁሌም ይርኛል።

ተጣፈ አሁን 19.58።
ስለምን ተጣፈ? ስለግራሞት ብቻ …



አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።