የሰማይ ቤት ሸንጎ አፈ ጉባኤያዊት።

      አሽካካች።
                                   ከሥርጉተ ሥላሴ 14.06.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዝዬ)
                „አቤቱ በመከራቸው ጊዜ ፈለግሁ፣ በገሰጽሠጽሃቸው ጊዜ ልመናቸውን ወደ አንተ አፈሰሱ።

                                            (ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ ፳፮ ቁጥር ፲፮“)

ጨረሯ ብቻ ደረሰኝ። ምን ደረሰኝ ብቻ አዳረሰኝ። እሷ ግን አትታይም። ስብሰባ ትሆንን? ወይንስ ሰማያዊ አልጋዋ ላይ ተኝታወይንስ ጫጉላ ጊዜ ላይ ትሆን ወይንስ ከባዘቶማዋ ፍራሽ ተኮፍሳ? ክብር ሲወድላት -- ደግሞም ሲያምርባትም የለችም። ብቻ የለችም። ግን አለች ትንፋሿ አገር ያዳርሳል። መንፈሷ ይሆን የሌለውይሆናል።  ምን ይሆናል ነው እንጂ። ግን ለምን? … እእለምን …. ለምን …?

ጠብቅኳት አልመጣችም። ለእኔ ለእራሱ የላከችው ለብ ያለ ጉድ ነው። ልም ነገር። ስትገርም። ለእናንተስ ይሄው የእኔ ዕጣ ፈንታ ደረሳችሁ ይሆን? … አላውቅም። ቀና ብዬ ፈራ ተባ እያልኩ ተመለከትኳት …    ነገ ሌላ ቀን ነው   አሃ! ብላ ጽፋለች።

ቀና ብዬ ስመለከት ደግ ይህም ያልፋል  ብላ ጽፋለች? ጎሽ! አልኩና ተረጋጋሁ።
ግን ለምን? አላውቅም። ለመሆኑ ያነብበኩትን እርግጠኛ ነውን? ነገ ሌላ ቀን ነው ብላ ስለመጻፏ እንደ ገና አዎን እንደ ገና አሻቅቤና ሻቅዬ  ሳዬው ተለውጦ

የማይቻለውንም መከራ ቢሆን በትእግስት ቻይው ብላ ጽፋልኛለች። ወይ ጉዴ ግንለምን? አላውቅም።ዝቅ ብዬ እንደ ገናአዎና እንደ ገና ተመለከትኩኝ።

ከመከራው በስተጀርባ ክብር አለ  በማለት ደግማ ጽፋለች። ምን ማለት ነው ይሄ ደግሞእሷን ብሎ ትንቢተኛ፤ እሷን ብሎ ስለነገ ራዕይ ተንታኝ - በታኝከደንቀራው ጋር ስትደልቅ ከርማ ባጅታ፤ ብዬ ላኮራፋት ዳዴ ስልላችሁ በአንድ አቅጣጫ የላከችው ጨረር ተባዛሳቀይንስ ተደመረ …   ተዳምሮ ተባዛና ተነሰራፋሞቅ አንደ ማለት ዳዳኝ። በጨረሮቿ ልክ የተደረደሩ ትዕይንታዊ ስንኞች ኪነን አንግበው ይታዬኛል። ጠጋ ብዬ ልዳስሳቸው ስል በቅጽበት - ቅጽበት ሆነው እርፍ።ግን እንደ ገና ተፃፈ። መነጠሬን ከኮሮጆዬ አወጣሁና በጥደፊያ ተያያዝኩት

አንዱ ምን ይል መሰላችሁወይ ጉድድድድድ …!የጨለማ ፀሐይ“     ይላል። ! አልኩኝምን ማለት ይሆን ይሄ? ---------------ብዬ ሳመናታ እራሱን ቀዬር አድርጎ ፈታልኝ  ፈገግ ብሎ   ህልም    ሲልእህህ! ብዬ ልቤን አዳመጥኩት። አሁን ወደ ቀጣዩ መልዕክት መሄድ እንደለብኝ ህሊናዬ ማስታወሻ ቢጤ ጫርጫር አድርጎ ላከልኝ። ቀጣዩ

   የሰማይ ቤት  ሸንጎ  የሚል መጣልኝ። ሃሃ! አልኩኝ።  ይህ ደግሞ ምን ይሆን? ብዬ ሳመናታ ሌላ አንድ - በአንድ ዘርዘር እያለ በጠብታ ከች  አለሳገጣጥመውየሞት አደባባይ  ብሎ ቁጭ። ውይ? ይሄም ደግሞ አለ? በጣም ፈራሁ። ጨነቀኝ። ተዘንፈዘፍኩ - ስላችሁ። አይጣል?

መነጠሬን ለማውለቅ ስታገልእሱ ደግሞ ለካስ ከዓይኔ ላይ ስበት ተፈጥሮለት አሻም እንዳለ ተሰክቶ ቅርት። ሲያናድድ። ተናደዱ እባካችሁ ከእኔው ጋር። ማስቲካ! ….ቀጥይ ማለቱ እንደሆነም ገባኝ። በምልክት ቋንቋበቃ አሸከረከረኝ እንደ ዛቢያ ስላችሁ። ገና እኮ ነኝ ወደ ሁለተኛው ጨረር አልሄድኩም። መዳህ ታውቃላችሁ ዝም ብሎ ታቱዥግራከወፌ ቆመች ያልተደረሰብልጭ ድርግም በሐመራዊነትአንተ ደግሞ ምን ልትል ይሆን ብዬ ዳጥም - ላጥም ይዞ ሊፈጠርቀኝ ግብግብ ስገጥምላችሁ …. አምላካችሁ አለ ሰውነቴ የማለውቀው ሆነብኝ። ዖዬ! እኔ ወይንስ ሌላ .. ህም

ተስፋ ይለመልማል  አይልም መሰላችሁ። ዎህ! ተመስገን። ወይኔ እኔና ተስፋ ከፊደል „ተ“ ከቃል „ተስፋ“ ስፈጠር ነው በፍቅር ድብን ብዬ እምወዳቸው። ፍንክንክ ፍልቅልልቅ ቧ ብራ ፏ አልኩኝ። ዋው! ደስ ሲል አልኩኝ። ይሄስ ምን ትርጉም ያስፈልገዋል ብዬላችሁ ወደ ሶስተኛው ጨረር ላዘግም ስሰናዳ  ውልብልቢቴን ጨምድዶ ያዝ አደረገናተስፋ ይጎድላል   ይቺ ናት እና ሥርጉተ …   አለኛ! እቴ የምን ጭንጫ ነገር ነው የኳረተ

መጀመር እንጂ ፍጻሜ የሌለው ሕይወትየራስህ ጉዳይ ነው። ፈንግጠው! ብዬ ቀጨር መጨሬን ሰባስቤ ስሰናዳያለዬለት የነበረው ቀለም እዬነጠረ እዬነጠረ መውጣት ጀመረአረንጓዴ ~ ቢጫ ~ ቀይ! ዋው፡~! እንኳንም ለሀገሬ አፈር አበቃህኝ ብዬ ጠላታችሁ ድፍት ይበልና ፍግም ብዬ፤ ክንብል ብዬላችሁ መሬቱን ልስም ስል   አትቸኩይ! የሀገርሽ ጉድ ገና ነው።    የሚል መልእክት በስተጀርባዬ …. ደለቀ።   ቁጣም ግልምጫም ድንፋታም ተዘልለው - ተዝልዝለው ምጥት፤ ህም!

አንኳኩብኝ …. እህ! አልኩኝና ደግሞ ምን ቀረ? ከማርያም መቀነት ወዲያ ስል አራተኛው ጨረር ፊት ለፊቴ በራልኝሰንደቁ በእግር ብረት ታስሯል  የሚል መልዕክት ፃፈ

ደሜ ሲንተከተክ ተሰማኝናእኮ እንዴት?! ስል በድፍረት ያነን የተላከልኝን አራተኛ ጨረር አፋጠጥኩትአሻቅቤ እያዬሁ በድፈርትና - በወመኔ ቁጣ፤ ፈንግጪው እንዳይለኝ ግን ስሜቴ ተክ --- ተክ ---- ትር ----- ትር ---- ብን ---- ብን --- ትን - ትን እያለ ነጋሪቱን ይጎስማል

እንቅልፋም! አሃ! ህም!  ተብሎ ተጻፍልኝ። ይህችን ትወዳለች ሥርጉትሻ፤ ኧረ እኔ ሆንኩኝ እንጉልቻም? ብዬ ያንኑ አራተኛ ጨረር ----- ላጥድፈው ፈራ ተባ ስል …. እኔ ትልቁ ችግሬ እንቅልፍ ማጣት ነው። መቼ ተኝቼ የማውቀውን ነው። ስጭር እኮ አኮ ነው ጉልት ብዬ እማድረው።ይህቺ ብዕር የሚሏት ቀለማም አድብታ ብክፉ ቀን አጠመዳኝ ሳለች ነጋ ጠባ ከእርሷ ጋር ነኝእያልኩ ስብተከተክ አምሰተኛው ጨረር ከች አለላችሁ። ጉድ!

ከዚህስ ወዲያ! … ¡¡¡“   የሚል በሥነ - ስላቅ፣ በትዝበት የቆዛዘመ ስንኝ ብቅ ጥልቅ እያለ አቅሌን መፈናፈኛ - ነሳት። ወይ አይጸድቅ ወይ አይነቀል። ወቼ ጉድ አልኩኝ። ማለት ነበረብኝ። ኧረ ባበቃልኝና ግልግል በሆነ ስል ተተካ ተረኛው፤ ትራስሽ ምን ግዴ ነው    ተባለኩኝ። ህም! „እሺ ምን ልሁን?

ምንስ ላድርግ? ይነገረኝእያልኩ ወኔዬ ገፍትሮኝ እዬተለማመጥኩኝ ስንተባተብላችሁ ስድስተኛው ጨረር …„አደብ - በሆደ ሰፊነት- ይመስጠር።  ሲል ውሽክ ብሎ ሽክ አድርጎ ፈታልኝ። ህም

በተፈጥሮዬ ጮኽ ብሎ መነገር አይሆንልኝ። ግጥሜም - አይደለም። አልኳችሁ ፊታውራሪ በር እንኳን ከልጅነት እስከ እውቀት አንድ ቀን ሰለቀችኝ - ቡጢዋን እልቻልኩትም ብሎ ችሎት ገትሮኝ አያውቅም፤ እንደተመሰጋገን ይሄው አለን። ግን ነገር ግን የአሁን አቤቱታ ቁሮ እንጂ የእኔ ማንነት አይደለም፤ እያልኩ ብቻዬን እያወጋሁ እጄን ከግራ ወደ ቀኝከቀኝ ወደ ግራ ሳወራጭ --- ላችሁመንፈሴ መሳሪያውን ሲያቀባብል - ሊተኩስ --- ተሰማኝዛሬ! ዛሬ! ዛሬ! ቁረጭ - ምረጭ! ለህዝብ ጠቀም ተግባር ሰባራ ሰንጣራን ከባህር ከገደል ጠቅልለሽ ከነዲሪቶው ጣይበይ! በይ!በማለት ወጥሮ ሰንጎ ለምን አይዘኝም መሰላችሁ።

እሺ ምን ልሁን ? ፈወስምንድን ላድርግ?“ እያልኩ እጅግ በሚያባብል በቁልምጫ፣ ህሊናን ዘና አድርጎ የጫጉላ ሽርሽር በሠረገላ ፈሰስ - ፈርሰስ በሚያደርግ ድምጽ ትህትናን አጋብቼ ድምፄን ለቀቅሰብሰብ …  ቀዳወዛሰበቅ  እያደረኩኝ በክብር አሽሞንሙኜ ቀና አልኩ። አዎን በተጠንቀቅም ጸጥ ረጭ ብዬ ቆምኩኝ። እንደባንዴራው። ከዛ አዎን ከዛማ ሰባተኛውን ጨረር ተላከ። እንዲህም ይላል፤ በጉልህም ኮቢውም ብራናውም ፈቅደውለት ተጥፏል።

ይበል …   የተግባር ስንቅና ትጥቅ ይኑርሽ  በማለት የጉዳዩን አናት በዕለተ ሰንበት ጸበሉን ትእዛዝ አሳወቀችኝ። ይሁን! እሺ! ብዬ ልሰግድ ጎንበስ ስልእርገት ውረድሰባቱም በአኃቲ ድምጽ
ቁረጪ! ትውልዳዊ ድርሻሽን ለመወጣት   ብለው ሲናገሩ በእነሱ ቅኔዊ - ቃናዊ ድምጽ መጉላት ጉልበታምነት መሰለኝከዙፋኗ ብቅ አለችና ብርኃኗን በመቁንን ሰደድ - አደረገችልኝ። እንዴት ነው ነገሩ ለብም አለደረገኝ። ከአንጀቴም አልደረሰም የብርኃን እናት ክብርት ልዕልተይ --- ሆይ! ስላት …“
በተስተካከለ ሙላት ለመኖር ሆኖ መገኘት + እዮባዊነት“  
     
                                      በማለት ከልቧ አዎን ክልቧ ☞ ከትከት ብላ አሽካካች … 

           ብሄራዊ ሰንደቅዓላማችን የሚፈታበት ንፍቅ አለኝ …. አብይ ሆይ እባክህን በቃህ በለው?
                                             የኔዎቹ ቅኖቹ ክብሮቼ መሸቢያ ጊዜ!


አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።