ልጥፎች

ከቻላችሁ ዩቱብ ቻናሌን ሳብስክራይብ አድርጉልኝ እስቲ፨

ምስል
    ማህበረ ቅንነት እንዴት ናችሁ፨   ከቻላችሁ ዩቱብ ቻናሌን ሳብስክራይብ አድርጉልኝ እስቲ፨ ዩቱብ ስለወቀሰኝ። ኑሩልኝ። ሥርጉትሻ። ·       https://www.youtube.com/channel/UCJEQXw86u_NG4A1FVC1j2qg  

እኔን የፈጠረኝ አምላክ እጥፍ ነው ቀድሞኝ የሚሄደው! የአንድ ሰው ህይወት የፍሬ ክፍል፡3 #comedianeshetu

ምስል

እንደዚህ አይነት እናት አይቼ አላውቅም ! በቆሸሹ ልብሶች መካከል ወዳጅነት ፈጠርን የአንድ ሰው ህይወት የፍሬ ክፍ...

ምስል

አነቃቂ መፅሀፍ ነው ? ወይስ እውነተኛ ታሪክ!! ይሄን እስከመጨረሻው የሰማ እምነቱ ይጠነክራል!! የአንድ ሰው ህይ...

ምስል

ልጄ የለም መባልን አያቅም ነበር ለሱ ብዬ የዳሮ ላባ እና የጥጥፍሬ ሰብስቤያለው ።#comedianeshetu #ins...

ምስል

የሆነውን ለመቀበል እና ለማመን ባንኮክና አሜሪካ ድረስ መሄድ ነበረብኝ!! ጀግና መፍጠር የትግስት #eshetu

ምስል

#እባካችሁ #ተለመኑን።

ምስል
  #እባካችሁ #ተለመኑን ።    ቃለ ምልልስ የምትሰጡ አታጋዮች ቢያንስ በቁጥጥር ሥር ስለዋሉት ወገኖቻችሁ ትንሽ እሰቡ። ምን ይሁኑላችሁ? ታስረዋል እኮ? ዕድሜ ልክ ይፈረድባቸውን? ወይንስ የሞት ፍርድ ወይንስ ይሰውሩላችሁ ምን ይሆን ፍላጎታችሁ? ሌላ በስልክ የምታገኟቸውም ቢሆኑ አጋጣሚን ልትቆጣጠሩት ስለማትችሉ ነገ ምን ሊፈጠር እንደሚችል አታውቁም እና ሥም ከመስጠት ታቀቡ። እባካችሁ ተለመኑን። እባካችሁ።   ከታሠሩ፤ ከተሰው በኋላ ማን አስታውሷቸው ያውቃልና? ቀንቷቸው ሲፈቱ ደግሞ እናንተው ቀዳሚ አዛኝ ሆናችሁ ትገኛላችሁ። ጋዜጠኛ ይጠይቃል። መብቱ ነው። ተጠያቂ ጥያቄው ይለፈኝ ማለትም ይችላል። መመለስ ግድ አይደለም። ሁሉ ተፈቅዶልኛል ሁሉ ግን አይጠቅምም። ከጀማሪ ታጋይ እንኳን አይጠበቅም በሁሉም ዘርፍሁሉም ካለው ሲሆን ያማል። አሁን እኮ እሳት ረመጥ ነው ያለው አገርቤት። በስልክ የሚሰጡ ትዕዛዞችም ከጥቅማቸው ጉዳታቸው ነው። እግዚአብሄር አምላክ የፈጠረልንን ማስተዋል አብዝቶ በልቦናችን ያስርጽው አሜን።   ስለ እስረኞቻችን ትንሽ ርህራሄ ይኑር። ቤተሰብ፤ ትዳር ልጅ ከሁሉምእናት አለች ያቺ መከረኛ። ሌላው ሁሉም በአቅሙ፤ በችሎታው፤ በፀጋው ብቻ ቢሳተፍ መልካም ይመስለኛል።   "የቤትህ ቅናት በላኝ።"   ጋዜጠኛ መሳይ መኮነን ስህተት የለበትም። የሌለበትን፤ ያልነበረበትን አወቃቀር እና ሂደት ለማወቅ ነው ጥረት ያደረገው ከሚያውቀው መረጃ ጋር አቀናጅቶ ለተነሳበት ዓላማ መስመር ውስጥ ለማስገባት። መታሰብ ያለበት ግንጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊም ሆኑ ምክትል ጠቅላይ ሚር ተመስገን ጡሩነህ ሙያቸው ስለላ መሆኑን ነው። ይህ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ የመጀመሪያ ክስተት ነው። ክስተቱ በተለምዶ ዘይቤ ሊታይ አይገባም። እጅግ ጥንቃቄ ይጠይቃል

አንተስ እንዴት ሆነህ ይሆን? ድንግልዬ አብራህ ትሁን። አሜን።

ምስል
  አንተስ እንዴት ሆነህ ይሆን? ድንግልዬ አብራህ ትሁን። አሜን። እናትህስ እንደምን ሆነው ይሆን? ድንግልዬ ትርዳቸው። አሜን። ውቦቼ ደህና ዋሉ፤ ደህና እደሩልኝ። አሜን። ሥርጉትሻ 14/04/2024  

#ክስተት #ለዘመን #ለራዕይም። #በተደሞ #ይመርመር። የመዳኛም #የፊደል #ገበታ ሊሆን ይችላል። ሰክኖ መመርመር። ይህ አዲስ ውሃ ያልነካው የተጋድሎ #ካሪክለም ነው። በአደብ ይመርመር።

ምስል
  #ክስተት #ለዘመን #ለራዕይም ። #በተደሞ #ይመርመር ። የመዳኛም #የፊደል #ገበታ ሊሆን ይችላል። ሰክኖ መመርመር። ይህ አዲስ ውሃ ያልነካው የተጋድሎ #ካሪክለም ነው። በአደብ ይመርመር።      "የዕውቀት ከንፈር ግን የከበረች ጌጥ ናት።" (ምሳሌ ፳ ቁጥር ፲፭)     ወጣትነቱን፤ መኖሩን፦ ዜግነቱን፦ ርዕሰ መዲናውን፦ ተስፋውን፤ ራዕዩን፤ ሐሴቱን፤ ምኞቱን፤ ትውፊት ትሩፋቱን፤ ወግና ባህሉን በሥርዓት እንዳይፈጽም፤ በባዕቱ በባድማውም መቀመጫ ያጣ ትውልድ እንዲህ ይቆርጣል። በእኔ የወጣትነት ዘመን የት ይደርሳሉ የተባልን ወጣቶች እንዲህና እንዲያ ሆነን ቀረን። ገና በጥዋቱ ነበር ቀዬወን ሰላም እንዳያሳጡ በ100 ቀናት ተግባራቸው ውስጥ ለጠሚር አብይህ አህመድ አሊ የገለጽኩት፤ ሂደት ላይም እያሉ በስፋት ዘርዝሬ ጽፌላቸው ነበር። ተማላ ሳሉ። እሳቸው አምቀው በያዙት የአስምሌሽን፤ የስውር ዲስክርምኔሽን የወረራ እና የመስፋፋት አብዝቶ የመጫን እና አማራነትን የመጠዬፍ ተግባራቸው ተጉ። ጆኖሳይድን አንቅረው በተፋው አገር ራውንዳ ሂዶ ከማስመሰል እሳቸው የጀመሩትን የትውልድ ምንጠራ ማስቆም ቀዳሚው ተግባር ነበር። ግን አልሆነም። የቆረጠ ትውልድ፤ መኖሩን የናቀ ትውልድ እንዲህ ሰማዕትነትን ፈቅዶ በሐሴት ያልፋል። ያውም በመንበረ መንግሥቱ መቀመጫ በአፍሪካ መዲና በአዲስ አበባ። የሚገርም ሰፊ የምርምር ተግባር የሚጠይቅ በጥሞና እና በተደሞ ውስጥ ለሚገኙ ሁሉ ፊደል ያስቆጠረ፤ አናባቢም ተነባቢም ክስተት እንሆ በምድራችን ተፈፀመ። አስፈሪም አጽናኝም፤ ፈታሽም አራሚም፤ ጎባጣ ሃሳብን አቃንቶ በሰከነ፡ በተረጋጋ መንፈስ ምንሽን ነው እማ ብሎ በማስተዋል ሊመረመር የሚገባው ክስተት። ይህ የጀግንነት ተግባር ተብሎ ሊታለፍ አይገባም። ለበቀል ብርንዶነትም

" ሽመላዊ ትምህርት "

ምስል
  " ሽመላዊ ትምህርት "     Yidnekachew Kebede "ሽመላ በመባል የሚታወቁት አዋፋት ወቅትን መሰረት ያደረግ ምቹ መኖሪያ ፍለጋ ከቦታ ቦታ ዝውውር ያደርጋሉ፡፡ በጉዟቸውም ልብ ብለን አስተውለናቸው እንደሆነ የ “V” ፊደልን ቅርጽ ሰርተው ነው የሚበሩት ፡፡ ሳይንስ የደረሰበት እውነታ ሽመላዎች በአንድነት ሲበሩ የሚኖረውን የአየር ግፊት ለብቻቸው ሲበሩ ከሚፈጥርባቸው የአየር ግፊት በእጅጉ ስለሚቀንስ ነው ፡፡ ብቻ ለብቻ ከሚበሩት ይልቅ የ “V” ፊደልን ቅርጽ ሰርተው በአንድነት ሁነው ሲበሩ የመብረር ፍጥነታቸውም በ71% ይጨምራል፡፡ ይህንን በመረዳታቸው ነው ሽመላዎች የ “V” ፊደልን ቅርጽ ሰርተው መብረራቸው፡፡ ሌላው ሊደንቀን የሚገባው ባሕሪያቸው በሆነ ምክንያት (በጉዳትም ሊሆንይችላል) አንድ ሽመላ ተነጥሎ ከዚህ ቅርጽ ከወጣ የተወሰኑት ተነጥለው በመቅረት በግራና በቀኝ በመሆን የሚደርስበትን የአየሩን ግፊት በማገዝ ወደ መንጋው እንዲቀላቀል ያግዙታል እንጂ ጥለውት አይሄዱም፡፡ እገዛቸውም የሚዘልቀው አገግሞ ከመንጋው እስኪቀላቀል ድረስ ወይም ደግሞ ለይቶለት እስኪሞት ድረስ የሚቀይ ነው፡፡ ሽመላዎች የሚያደርጉትን እረዥም ጉዞ ይመራ የነበረው ሽመላ በደከመው ጊዜ የመሪነት ሚናውን ለአንደኛው ያስረክብና ከኋላ በመሆን እረፍት ያደርጋል፡፡ ሽመላዎች በሚጓዙበት ወቅት ቋቅ… ቋቅ... የሚል ድምፅ ያስተጋባሉ፡፡ ይህም በገጠሩ የሀገራችን ክፍል እንደሚደረገው የደቦ ሥራ ሽለላ ጎዞውን ተበረታታው በነቃ መንፈስ እንዲጓዙት ለማድረግ የማነቃቂያ ስራ ነው፡፡ በተለይም ደግሞ ፊት ሆኖ መንጋውን ለሚመራው ግብረገባዊ ትምህርት ተፈጥሮ በራሷ ይንን ይረዱት ዘንድ ለሽመላዎች ጥበብ ሰጣቸዋለች፡፡ እኛም ከእነሱ ተምረን በአንድነት መስራት

#ሬሳ ሽምግላ ላይ ነው። ቬርሙዳው ሎሬቱ ይቀጥላሉ። 12/04/2023 #አንሰበርም።

ምስል
  #ሬሳ ሽምግላ ላይ ነው። ቬርሙዳው ሎሬቱ ይቀጥላሉ። #ግርባው ብአዴን ከመቃብር ውስጥ ሆኖ ፊሽካ እዬነፋ ነው። ቅልጥመኛውም ከዲሲ እስከ ኦነግ ቤተ መኔግሥት ተዘርግቷል። ተንቦርንሻ እትብቱን ለማዳን ሸር ጉድ እያለ ነው። #ግራብው ብአዴን፣ #ኦሜኮ ወለጋ ሄደው ጽህፈት ቤታቸውን ይክፋቱ። ለሰከንድ የመንፈስም የአካልም ምርኮ እንዳትቀበሉ። አስፈንጥሩት። ዬእኔ አባ ትግሥት ጨምተህ ትግልህን አጠናክር። ማቃጠል ጥሩ አይደለም። ብዙ ሰላማዊ ትግል አለና። ሰማዕትነት ለዘላቂ የአማራ ክብር፣ ለብቁ የአማራነት ልዕልና ይሁን። በዚህ አጋጣሚ ቤቱ ፈርሶበት ለመኖር ሄዶ የተሰዋ ሰማዕትም አለን። ዬእኔ አባ ቅንዬ አማራዬ ፀንተህ ለሥር ነቀል ለውጥ ታገል። ዬሰማዕታት ቤተሰቦች መጽናናትን እመኛለሁኝ። በንፁኃን ላይ የፋሺዝም ሂደት ይቀበርበታል። ብቻ ጥበብ፣ ትእግስት፣ መረጋጋት ይሁን እሺ ይባል። ሽምግልና አትቀየጥ። ቤትህ ቁጭ ብትል፣ ግብር መክፈል ብታቆም በዝምታ ብዙ ድል ይገኛል። ይህ መከራ ብሶ ስለሚቀጥል ማንንም አምነህ ተላላ እንዳትሆን። አደራ። ሄሮድስ አብይ ሙሉ ጎንደርን ለሱዳን ሊሰጡ እንደሚችሉ ሁሉ እሰቡት። መቅጫው አሳቻ ነው። መስዋዕትነቱን የሚቀንስ ተጋድሎ ያስፈልጋል። ፋኖ ልዩ ኃይል ካንፕ እንዳትገቡ። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 12/04/2023 #አንሰበርም ።

አሚኮ ከሚባል #ኦሚኮ ይባል። 12/04/2023

ምስል
      አሚኮ ከሚባል #ኦሚኮ ይባል። ሙሉ አምስት ያዬሁት ዝልብልብ አመክንዮ ይህንኑ ነው። በዳብል የሚሠራው ለገዳ ወረራ፤ ለገዳ መስፋፋት፤ ለገዳ አስምሌሽን፤ ለጋዳ ዲስክርምኔሽን ኢትዮጵያ በነፃ እንድትነቀል ነው። በማህል ያሉ ጠቃጠቆ መልካም ነገሮች ቢኖሩትም። ጠቅልሎ ገዳ ውስጥ የተዘፈቀ። እግዚአብሄር ይስጥልኝ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 12/04/2023 ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው።

አማራዬ

 አማራዬ ለፍሪንባ ፍርፋሪ ለቃሚ በርህን እንዳትከፍት። አደራዬ ጽኑ ነው። አሁንም ደራጎን አፋን ቧ አድርጎ ሊያስውጥህ አዘናግቶ ጥቃትን ሊሸልምህ ተሰናድቷል። በጥንቃቄ ተራመድ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 12/04/2023

ዕውነት የመኖር ሐዋርያ ነው።

ምስል
 ዕውነት ራሱን ክዶ አያውቅም። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 12/04/2022  ዕውነት ዕውነታዊ አመክንዮን ሸሽቶም፣ ተሸሽጎም አያውቅም። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 12/04/2022  ዕውነት ለዕውነት መንገድ ዘግቶበት አያውቅም። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 12/04/2022  ዕውነት ንፁህ፣ ዕውነት ፃድቅ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 12/04/2022  ዕውነት የመኖር ሐዋርያ ነው። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 12/04/2022    

ኢትዮጵያስ እንደምን እያሆነች ነው ይላል።

ምስል
  ዕለተ ሰኞ ዕለተ ጠባቂ በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ሕይወት ብራ ለራህብ የሚራራ። „ዝም ብዬ የመከራን ቀን እጠብቃለሁ።“ (ትንቢተ ዕንባቁም ምዕራፍ 3 ቁጥር 17)     ዕለተ ሰኞ ማዕዶት ጠባቂ ሁሉም አጀንዳ የሚሰናገድበት ዕለት ነው። መንፈሴ በይ ያለኝን ሁሉ ያለገደብ የሚኮለምበት። ዛሬ የቀናው አጀንዳ እንዴት ሰነበታችሁ? ሰንበት እንዴት አለፈ? ኢትዮጵያስ እንደምን እያሆነች ነው ይላል። • 365 x 3 = 1095 x 24= 26,280 የቁጥር ተማሪ አይደለሁኝም። በቁጥር ትምህርት እጅግ ደካማ ነበርኩኝ። ስለዚህ ስህትት ሊኖርበት ቢችልም እርዕሴ አይፈረድበትም። እኔ የባይወሎጂ እና የኬሚስትሪ ጎበዝ ተማሪ ነበር የነበርኩት፤ እንዲያውም 11/12ኛ በደረጃ ነበር ተሸልሜ ያለፈኩት። የሆነ ሆኖ ወደ ዕርዕሰ ጉዳዬ ምልሰት ሳደርግ ሰውኛ ኢትዮጵያ ውስጥ በዬደቂቃው አደጋ ውስጥ ነው። ህዝብ እያለቀ ነው። ሞቱ ብቻ አይደለም በስጋት እና በሽብር ኢትዮጵያዊው ሰው ከጽንሰት ጀምሮ እዬተረሸነ ነው። ሰው አለን ለማለት አንችልም። እንዲያውም እኔ ቤት ሆኜ ሳስበው ኢትዮጵያ ውስጥ ምን ያህል የሥነ - ልቦና ባለሙያ ይኖር ይሆን እላለሁኝ። መጪው ጊዜ መርግ ነው። ችግሩ አልተጀመረም ብዬ ነው እማስበው። • ምክንያቱም … ከአጤ ዝናቡ ከጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ጀምሮ የሥነ - ልቦና ህመም የለብኝም የሚል ሊኖር ስለመቻሉ እርግጠኛ አይደለሁም። እያንዳንዱ ደቂቃ በደም ውስጥ ያለፈ // ያለም ነው። እያንዳንዱ ደቂቃ በጭንቅ ውስጥ ነው የሚያልፈው// ያለም። „ከእኛ የሚሞተው ከሌላ አገር ጋር ሲነጻጸር ትንሽ ነው“ ባይ ሄሮድሳዊ መሪ ያላት አገር ናት - ኢትዮጵያ። „ግብጽ ጦርነት ትጀምር ብዙ ስራ የሌላቸው ደሃ ልጆች አሉን ለማገዶ እምናቀርባቸው