ስለምን ይሆን የኢትዮጵያ ፖለቲካ #አጽናኝነትን እንደ ጦር የሚፈራው?

 ስለምን ይሆን የኢትዮጵያ ፖለቲካ #አጽናኝነትን እንደ ጦር የሚፈራው? 

ለምንስ ይሆን #አይዟችሁ #ባይነት እንደ ወንጀል የሚታዬው? 


በኢትዮጵያ ፖለቲካ #ሰዋዊነት #አደጋ ውስጥ ነው። 

ይህ አካሄድ ጨካኞች፦ በጭካኔያቸው ጀግንነት እንዲሰማቸው የሚያደርግ ነው። 

የኢትዮጵያ ፖለቲካም ለጨካኞች ሽፋን ስለሰጠ የፖለቲካው አውራ መሪ እኔ ነኝ፤ ሥራም ሠርቻለሁ ይላል። 

ፖለቲካ ሠሪው #ሰው ነው። ፖለቲካ የሚሠራውም #ለሰው እና #ለተፈጥሮ ነው። 

ስለሆነም #ሰውኛነት ቢያስመሰግን፤ ቢያስከብር እንጂ በኢትዮጵያ የፖለቲካ ህግ #መሳደጂያ ሊሆን አይገባም። 

የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከሰውኛ ማዕቀፍ ውስጥ #ያፈነገጠ ነው። 

ይህን ማረቅ እና ማሰተካከል ይገባል። #ሃግ ሊባል ይገባል። የኢትዮጵያ ህዝብ በተፈጥሮው አዛኝ፤ ሩህሩህ፤ ደግ እና አጽናኝ ነው። 

ሃዘኑን በወል በህብራዊነት አስከብሮ የኖረ ህዝብ ነው። 

ይህን #ጸጋውን #የሚገፍ #አሳቻ ዘመን ላይ ነውና በጥሞና የኢትዮጵያ ህዝብ ሊያስብበት ይገባል። ገዢወቹንም ሊያርማቸው፤ ሊገስፃቸው፤ ሊቆጣቸው ይገባል። 


ሥርጉትሻ2025/03/26

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

የእኔ እማ ልዕልቴ እንዴት ነሽ?