እቴጌ መቀሌ 0k17.2019

ህም። ነው ዘንድሮ። እቴጌ መቀሌ ጦርነት አውጃ፣ ጁቡቲን ሱማሌ ላንድ ሌላ ጥቃት ሰንዝረው፣ ጎንደር ከተማ ዙሪያውን ቀውጢ ሆኖ፣ ድሬ እና ሀረር ጎረምሶች እዬመሯት፣ አጣዬ እና ኬሚሴ ሌላ ጦር ታውጆ፣ አዲስ አበባ በጭንቀት ተወጥራ፣ አዳማ፣ ደብረዘይት በጎረምሳ እዬታመሱ፣ የውህድ ፓርቲ ዘፈን ይደለቃል። መሬት እኮ ልትፈነዳ ተቃርባለች። እራሱ መከላከያ በዬዞጉ ጎድቯል ወይንስ ልቡ ከኖቤል ተሰክቶ ይሆን? ይህም አይታወቅም። ይህም አይደመጥም። ይህ ሁሉ ታምቆ ቤተ መንግሥት አንድ ጊዜ ከካቢኔው ሌላ ጊዜ ከኦዳ ዛፍ ጋር ፈንጠዝያ ላይ ነው። የዲፕሎማት ማህበረሰብም አንድ ነገር ቢፈጠር መውጫችን ብለው ያሰቡት ነገር የለም። ሌላም መገዳደል ይኖር እላለሁኝ የኦዳውን ዛፍ አስተውዬ በአርምሞ እያዬሁ። ይጨንቃል። ያስፈራል። ፀሎት።

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።