ልጥፎች

ዘመነ ኦዳወገዳ ቀውሱ የተቃኜበት የዛሬ 09.06.2022 የፀጋዬ ራዲዮን ከ15.00 -ከ1600 በራዲዮ ሎራ ላይፍ ...

ምስል
ደመከሴ አበለ ግጥም ነው። መጨረሻ ላይ ተካቷል። የዛሬ 09.06.2022 የፀጋዬ ራዲዮን ከ 15.00 - ከ 1600 በራዲዮ ሎራ ላይፍ ላልተከታተላችሁ እንሆ። የአማራን ሙሉ አቅም ለአማራ የማንነት እና የህልውና ተጋድሎ ብቻ የሚያውል ተፈሪ ማንነት መፍጠር ስለምን ተሳነን ጭብጡ ይህ ነው።

የፀጋዬ ራዲዮ 12 05 2022

ምስል
የዶር ደብረጽዮን ጥሪ ለአማራ ህዝብ ቅድመ ሁኔታ።

የፀጋዬ ራዲዮ የዕለቱ መሰናዶ ይህን ይመስል ነበር። 26.05.2022

ምስል
·        የፀጋዬ ራዲዮ ችግር ገጥሞት ባጅቷል።   የመኖሪያ ቤቴ ስልክ እዬከፈልኩበት ከዘጋሁትም መንፈቅ አለፈው። መኖሪያ ቤቴን በጫና ለማስለቀቅ ከፍተኛ ዘመቻም አለ። ሥርጉትሻ ጠበቃ ይዛ መሞገት ትችላለች። ጠብ ሲኖር ዞር ነው የእሷ ተፈጥሮ። የጸጋዬ ራዲዮ መረበሽ የአፍሪካ መሪወች፤ የአርቲስት ቴወድሮስ ልቅና፤ የዬኔታ ጎዳና ያእቆብ እና የዲያቆን አባይነህ ካሴ ጥምር ስለ ኢትዮዽያ ያላቸው ጥልቅነት መግቢያ ስላደረግኩት ኦነግ ሁሉ ነገር ስለሚረብሸው ብዬ ተውኩት። ረብሻዉ ለሁለት ወር ጋፕ ብሉ ቀጠለ። ያለፈው ፕሮግራም 12.05.2022 ሙሉው ነበር ቅስሙ የተሰበረው። እኔ ከቤት ሆኜ የፕሮግራሙ ኃላፊና ቴክከሩ ተከታተልነው። ህውከቱ የሚጠገን አልነበረም። ኢትዮጵያን የማፍረስ ያህል ነበር። ዛሬ ፕሮግራም ነበረኝ። ልክ ረብሻው ተጀመረ ከዛ ቀጠለ። እንደ እኔ ቲሙ ይከታተለው ስለ ነበር 15.44 ደቂቃ ቀጣዩ ዝግጅት ለ5 ደቂቃ 15.49 -16.00  ቀጠለ ከ 16.00 እስከ 16.18 የተቋረጠው ሙሉው ዝግጅት ቀጠለ። በሌላ ዝግጅት እንዲህ የለም። ኢትዮጵያን የማፍረስ አላማው እንዲህ ዝልቅ ነው። ዘመኑ ያልገባውፖለቲከኛ « ተረኝነት» እያለ ልባችሁን ያወልቀዋል። መከራው ጥልቅ ነው። ለመከራው የሚመጥን ፖለቲከኛ የላትም ኢትዮዽያ እኔ የጸጋዬ ራዲዮ ቢዘጋ ጉዳዬ አይደለም። ከመጠን በላይ ሠርቻለሁ። ደክሜለሁ። አመሰግናለሁ ተብዬ አላውቅም። ደክሞኛልም። ብዙ ጊዜ አይሆኑ ሆኜ እማስገቸው ስኬቶች ሌሎች ሲወዳደሱበት ቁጭ ብዬ አያለሁኝ