ልጥፎች

አንዲት መንገድ አለች ከምድረ በዳ ውኃ የማታስለምን። የአቤልዕንባ ጠብታ። አብን የአማራው አቤል ድምፅ ነው።

ምስል
እ ንኳን ወደ ከ በቡሽ ል ሳነወርቅ ብሎግ በሰላም መጡልን።   አንዲት መንገድ አለች ከምድረ በዳ ውኃ የማታስለምን። የአቤልዕንባ ጠብታ። አብን የአማራው አቤል ድምፅ ነው። አብን የስለትም ልጅ ነው። " እግዚአብሔር በአንድም በሌላም ይናገራል፤ ሰው ግን አያስተውለውም። "     # ጠብታ ። የንገረው አዲስ ድምፅ ጎጃም፤ ወላሂ ሁለተኛ አማራ አልሆንም ወለጋ፤ እናቴን ድውድው አደረጓት ደቡብ ጎንደር፤ ወዋ ጎቤ እና ቲሙ፤ ስንቱ ደመ ከልብ ሆኖ የቀረ የአማራ ደም ይጮኃል። ከዬት እንደምጀምር አመናታሁኝ። እርዕስ ጽፌ መፃፍ አልችልም። እርዕስ ቢሰጠኝም አልችልም። አካል ከሌለው ቃለ ወንጌል ልነሳ። # ቤት አፍርሶ መንገድ ላይከመውደቅ ፈጣሪ ይጠብቀን። አሜን። የአዲስ ድምጽን ተከታታይ ቃለ ምልልስ ጥሩ ጊዜ እዬመረጥኩ አዳመጥኩት። ጥሩ ውይይት ነበር። በሳል ልጆች አብን አለው። የሰከኑ መንፈሶች አይቻለሁኝ። ቲምሊደር ላይ ይሆን ችግሩ ብዬ አሰብኩኝ። እሱ ብቻ ሳይሆን # የአሳቸው ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ አሊ ንጥቂያም አለ። የመንፈስ ዘረፋ። የአቅጣጫ ቀያሽ ምህንድስና። እራሱ አማራ ብሎ መጀመሩ አይመቻቸውም። # በቃ ማሰብ። ምክንያቱም አማራ ምን አለው ? ማን አለው ? ዕውነቱ ምንም፤ ማንም ነው። ኢትዮጵያ ውስጥ አሁን ያለውም ይሁን እተካለሁ የሚለውም ይሁን በቁጥር አንድ ለአማራ ህዝብ አንዲት መንገድ ብቻ ናት ያለችው። ጥብቆ መንገድ። ያም አብን ተሟሙቶ ማስቀጠል።