ልጥፎች

ህሊና።

ምስል
         ህሊና። ከሥርጉተ - ሥላሴ  ( Sergute © Sselassie ) 10.01.2018 (ከጭምቷ - ሲዊዘርላንድ።) „ትሁት ልብ የሥጋ ሕይወት ነው፤ ቅንዓት ግን አጥንትን ያነቅዛል።“  (መጸሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፲፬ ቁጥር ፴) ·                      እ ንደ መነሻ https://www.youtube.com/watch?v=lzMC2C1x0Qw ESAT Efeta 5 Jan 2107 (2018 ) http://www.satenaw.com/amharic/archives/44372 „ ይድረስ ለአቢይ አህመድ ( ዶ / ር  ( ለኦህዴድ ፅህፈት ቤት ሀላፊ በኤርሚያስ ለገሰ)                  ቆንጽሎ ማዬት የጭንቀት በሽታ ነው። ዛሬ ትንሽ ከፖለቲካ ተንታኙ ጋዜጠኛ ኤርምያስ ስጋትን ማነሳሳት እንዲህ አሰኘኝ። ይሳሳ - ይባዘት - ይቀንደብ፤ የማከብርህ ወንድሜ ጋዜጠኛ ኤርምያስ ለገሰ እንዴት ሰነበትክ? ምነው እንዲህ ብትክትክ አደረገህ? አንድ ጊዜ ከእነከሌ ጋር ጎን ለጎን መቀመጥ የለባቸውም ትላልህ፤ ከተጨባጭ ውጪ የሆነ ነገር። አሁን ደግሞ ኦፌኮን ምህረት ይጠይቁ ትላለህ? ግራው ገባህ።  እንደዚህ ከሆነ አትደራጁም ብላችሁ ጦር የሰበቃችሁባቸውን የአማራ ድርጅቶችን ይቅርታ ጠይቁ - እናንተም። የአማራን ተጋድሎ „የነፃነት ሃይል እያላችሁ“ ሥነ - ልቦናችን ባልተወለደ አንጀታችሁ ያረሳችሁትን ሁሉ ቁስሉ እንዲሽር ይቅርታ ጠይቁ። ከገዳይ ጋር የጎንደር ፋሲል ግንብን የዜና ሽፋን በማድረግ ጎንደሬ በሙሉ በገዳይ ስዕል ውስጥ የተቀረጸውን መንፈስ ይቅርታ ጠይቁ።  ለነገሩ ፋሲል ግንብ እኮ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያለው ቅርስ ነው። በዚህ ቢኬድ ጦሱ የሚገፋ አልነበርም። መንገዱ ጠ

አብይ የጎንደር ብቸኛው ጌጥ! ክፍል ሁለት፤

ምስል
               አብይ ኬኛ!   ለቅኖች ብቻ!  ክፍል ሁለት፤                       አብይ የጎንደር ብቸኛው ጌጥ!                                     ሥርጉተ ሥላሴ  ( Sergute © Sselassie ) 24.12.2017 (ከጭምቷ - ሲዊዘርላንድ።) „አቤቱ ከንፈሮቼን ክፈት፤ አፌም ምስጋናህን ያወራል።“    (መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፶ ቁጥር ፲፭ ) ጋዜጠኛ ማስረሻ አለሙ „ ማማ “ በሚለው ዝግጅቱ „ከመለሳውያን ወደ ለማውያን“ በማለት እራፊ ጨርቅ ሳያክልላቸው ካብጠለጠላቸው „ለማውያን“ ወጣት የፖለቲካ ሊሂቃን መካከል ዶር. አብይ አህመድ አንዱ ናቸው።  ጋዜጠኛ ማስረሻ አለሙ ዶር. አብይ አህመድን የቀረጸበት መንገዱ በራሱ ሃሳብ ውስጥ መቆም የተሳነው፤ ውራጅ ፖለቲካን የሙጥኝ ያለ፤ ዘልዛላ ሰብዕና አላብሶ ነው ያቀረባቸው። አምላኬ ይቅር ይበለው። ይህ የተለመደ መንገድ መሆኑ ቢገባኝም አሽኮኮ አድርጎ መኖሩ ግን የገለማኝ ስለሆነ አሁንም በተከታታይ በዚህ ዙሪያ እሞግተዋለሁ።  አቅም ብቅ ባለ ቁጥር እንዳይበቅል፤ እንዳይጸድቅ ከዝንተአለም መከራ ሳይሆን በሞት ውስጥ መኖርን ላልተፈቀደለት ዕንባማ ህዝብ የማይበጅ መንገድ በመሆኑ በትጋት መፋለም ይገባል። እርግጥ እሱ የቤተ - መንግሥት ሜዲያ አዘጋጅና አቅራቢ ጋዜጠኛ ስለሆነ ባለ ዓለምዐቀፍ ሚዲያ ነው።  እኔም እንደቅሚቲ በሳተናው ብራና ሚዛኑን ማስጠበቅ ይገባል ባይ ነኝ።  ጋዜጠኛ ማስረሻ አለሙም ከቤተ- መንግሥቱ መንበር ወረድ ብሎ ታች ትቢያ ላይ ያለነው ጥቁር ለባሾችም ደግሞ ምን እንደሚሰማን ማወቅ ይኖርበታል - ተገዶ። መቼስ ሁሌ እንደተጠንጠለጠሉ አይኖርም። መውረድም መውጣትም ሂደት ነው …. ·          የሃሳብ ተክል።