ልጥፎች

የዳግማዊ አባ ኮስትር አቶ ንጉሡ ጥላሁን እና የይደንቃቸው ከበደ ውልፍትና ፍጥጫ!

ምስል
ዳግማዊ አባ ኮስትር  ምንይል? „አቤቱ በዓመታት መካከል ሥራህን ፈጽም፤ በዓመታት መካከል ትታወቅ በመዓት ጊዜ ምህረትን አስብ።“ (ትንቢተ ዕንባቆም ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፪) ከሥርጉተ©ሥላሴ 20.07.2018  ( ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ) መታዬት ያለበት ቪዲዮ። ልባምነት። የማከብራችሁ ክብረቶቼ ይህን የቪዲዮ ክሊፕ እዩት እና  ፌስ ቡክ ያላችሁ ሸር  አድርጉልኝ። ከዘራፊ ጋር መደመር ወንጀል ስለሆነ። ሥራ ከሚቀፈው ፋውል እና ግን ከሞቀ ከሚጣደው ጋር መደመር ይከብዳል ብቻ ሳይሆን ይቀብራል።  https://www.youtube.com/watch?v=uVp9w1x_Gn0&t=148s ETV  ለታሪክ   ዘራፊዎች   ማንዘርዘሪያ   ሊኖረው   ይገባል።   የአማራ   ተጋድሎ   ታሪከ   ከልብ   አይደለም !  ምንጊዜም   ያሽታል ! (19.07.2018.) ·        መንተራሻ ! እንዴት ናችሁ የኔዎቹ … አጅግ የሚገርሙ ፖለቲካዊ ቀውሶችን መፍጠር ዋነኛው ስልት ነው የልግመኛው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ስተራቴጂ መስፈርት ይባል ታክቲካዊ መንገድ ይባል አላውቅም የኔዎቹ ባሻችሁ መልክ ተቀበሉት። የሆነ ሆኖ ሰማያዊ ፓርቲ ቤተ መንግሥት አካባቢ ድር እና ማግ የመሆን ህልም ወፍ ያወጣው ገጠምኝ አግኝቷል።  ማን ይህን መሥመር ዘረጋለት ለሚለው እኔ አውቃዋለሁኝ፤ ለጊዜው ግን በአባ ዝምታ ይቆለፍ። ያው ሴቶች ትንሽ በእንደነዚህ ዓይነት ጉዳዮች ቀደም ያሉ ዕይታዎች አሉንና። በተለይ በቀደመው ጊዜ የኢትዮጵያ መንግሥት ባይባልም በወያኔ ሃርነት ትግራይ ሥርዕዎ መንግሥት ዘመን አቶ ልደቱ አያሌው እንደ ነበሩ ይታወቃል የሚዲያው ባላበት ባለሙሉ እንደራሴ።  ሁሉንም የፖለቲካ ድርጅቶች

ታሪከ ብራና ከክፍል አንድ አስከ ስድስት!

ምስል
የአቡነ ሳሙኤል ዘዋልድባ ታሪክ ከክፍል አንድ እስከ ስድስት።      „አቤቱ ጣልኽን አፈረስንኽም፤ ተቆጣኽን ይቅርም አለኽን።“ (መዝሙር ምዕራፍ ፶፱ ቁጥር ፩) ከሥርጉተ ሥላሴ 19.07.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ) ·       መቅድም። ይህን የዋልድባ አብርንታት ገዳም የተወሰነውን ክፍል እንድተርክ ያስገደደኝ ዶር አብይ አህመድ የሳይንስ እና የቴክኖጂ ሚ/ር በመነበሩበት ጊዜ „ከርምጃ ወደ ሩጫ“ የሚል ሞቶ ብሄራዊ ጉባኤ አሰናድተው ነበር። በዛ ብሄራዊ በሆነ ጉባኤ ላይ ልዩ የሆነ መንፈሳቸው በኢትዮጵያዊነት ንጽንህና የተቀዱሱ ኢትዮጵያዊ ሊቃናት የተሳተፉበት ፍጹም ንጹህ ጉባኤ ነበር። ያው የጹሑፌ መደበኛ ተካታታዮች እንደምታውቁት የኢሳቱ ጋዜጠኛ አቶ ማስረሻ ዓለሙ „ከመለስውያን ወደ ለማውያን“ የሚል አንድ ፍጹም የሆነ ጥላቻን ያነገሰ፤ ሰብዕናን የተደፈረ፤ እንዳትቀበሏቸው የሚል ጠንከር ያለ የለማ እና የአብይን መንፈስ እንደ ግል እንደ ድርጅትም ኦህዴድን የተጻጸረረ ዝግጅት ነበረው። ያን ጊዜ ወደ 22 ሺህ አድማጭ ተከታትሎታል። እዚህ የውጭ አገሮቹን ጨረሱ እና አገር ቤት ደግሞ ቡቃያ ብቅ ሲል የሰላ መዶሻቸውን እነ የተባበሩት ይዘው ወጡ … መቼም አይታክታቸውም ቡቃያ መንቀል፤ ቅናዊ ጉዞን ማገት …  ·       ፍቅራዊነት እና ኢትዮጵያ። እኔ ደግሞ ዶር አብይ አህመድ እና ዶር ምህረት ደበበን በንጽሁ ህሊናን አደረጃንት፤ እንዲሁም ዶር ገምቺስ ደስታን  በብልህ አመራር እና አስተዳደር ሳይንሳዊ ትንተና ቀደም ብዬ ለፍቅራዊነት ፕሮጀክቴ አህጉራትን ሳስ አፍሪካ ላይ ነፍስ ያለው ተግባር የሚከውኑ ስለመሆኑ መረጃ አገኘሁኝ። በዚህ ስሌት በህሊናዬ ውስጥ ለእነኝህ የመልካምነት ብቃት ብልሃት መምህ