ልጥፎች

የአገር ፎለቄ ፈርጥ እንደ አልባሌ?

ምስል
የአገር ፎለቄ ፈርጥ እንደ አልባሌ? „ወገኔ ሆይ አድምጠኝ፤ ሕዝቤ ሆይ፣ ስማኝ ህግ ከእኔ ይወጣልና ፍርዴም ለአህዛብ ብርሃን ይሆናልና።“ ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ ፶፩ ቁጥር ፪ ከሥርጉተ©ሥላሴ  Sergute©Selassie 07.01.2018  ከእመ ዝምታ ·        እፍታ ለአንድ አፍታ! ውዶቼ እንዴት ናችሁ ደህና ናችሁ  ወይ? ዛሬ ቀጠሮዬ ሳልባክን  የጠ/ሚር አብይ አህመድን ከመምህራን ጋር ያደረጉትን ውይይት በጥሞና ላደምጥው ስለፈለግኩኝ ሦስቱንም ክፍል በበዛ ጥሞና ታደምኩበት። ያው ለእኔ እንደ ትምህርት ክ/ ጊዜ ስለማዬው ማስተዋሻ እያያዝኩኝ ነበር ያደማጥኩት። የ ሚገርመው የፕሬስ ሰክሬታርያት ጽፈ/ቤት ሃላፊዎችም፤ የጠ/ ሚር/ ቢሮ የጽህፈት ቤት ሃላፊ ማስተዋሻ እንኳን አልያዙም ነበር። ታዳሚዎች ግን ሲይዙ አይቻለሁኝ። ይህም አንድ የሾለክንበት ጉዳይ ነው። ትውልዱ ከእኛ ምን ይማር? በተገኘው አጋጣሚ ሁሉ ትውልዱን እያሰቡ ቢሆን መልካም ነው። ልጆች ከሚሰሙት ይልቅ በሚያዩት ይመሰጣሉና።  የሆነ ሆኖ በዚህ ጠ/ሚር አብይ ባደረጉት ንግግር ለተነሱ ጥያቄዎች በሰጡት መልስ በጥልቅነት ውስጥ የመታደላችን ልኩንም በልበ - ህሊና ለመለካት ሞከርኩኝ ። አስተውሉ የኔዎቹ ሞከርኩ ነው ያልኩት። ስለምን? ይህን አልኩኝ መሰላችሀ ... የሳቸውን የተመስጦ ይዘት ለመተርጎም የዕድምታ ሊቃውንትን ስለሚ ጣራ ። ከዕድምታ ሊቃውንትነት ጋር ይተካከላሉ ብዬ እማስባቸው ፕ/ ዶር ፍቅሬ ቶሎሳ ስለሆኑ የቤት ሥራውን ለሳቸው ልተዎው። ግን ስንቱን ይዘልቁታል? ንግግሩን እያዳመጥኩኝ በቀደም ዕለት ሙሉ ቀን ያሸኝን የሻ/ ዳዊት የእናፍርስ ብሄራዊ ጥሪን ስለምን ደከምኩበት አልኩኝ። ምክንያቱም

ቸርነቱን ለቸሩ።

ምስል
ቸርነቱን ለቸሩ። „ወርቅ እና ቀይ እንቁ ግን ይገኛል፤  የዕውቀት ከንፍ ግን የከበረች ናት።“ መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፳ ቁጥር፲፭ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 08.01.2019 ከእመ ብዙሃን ሲዊዝ።                                                              አባ ቅንዬ!     ሙሉ ጤንነት ከሙሉ ሰላም ጋር ቀንበጥ ትመኛለች ለዶር ለማ መገርሳ   ለዴሞክራሲ አባት። ለጸሎት እንትጋ! ኑሩልኝ።  

ይድረስ ለማከብረዎት ለብ/ ጄ/ አሳምነው ጽጌ ።

ምስል
ይድረስ ለማከብረዎት ለብ/ ጄ/ አሳምነው ጽጌ ባህርዳር። „ወርቅና ብዙ  ቀይ እንቁ ይገኛል የእውቀት  ከንፈር ግን የከበረች ጌጥ ናት።“ መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፳ ቁጥር ፲፭ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 08.01.2018 ከእማ ዝምታ - ከሲዊዝሻ።                                                                 ·         መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=Swe0gQaJ8FU ETHIOPIA - '' አርበኞች ግንቦት 7 የውሸት ፖለቲካ እየተጠቀመ ነው። ' ' ቅሬታ አቅራቢ የግንባሩ ወታደር - NAHOO TV Nahoo TV Published on Jan 5, 2019 ጤና ይስጥልኝ የማከብረዎት ብ/ጄ አሳመንው ጽጌ እንዴት ሰነበቱ? ደህና ነዎት ወይ?እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በሰላም አደረሰዎት። መታመን እንዳይደርቅ አስቸኳይ ምላሽ ቢሰጥበት መልካም ነው ለጥያቄዬ ... ከዚህ ሩህሩህ ዘመን በላይስ ምን ይናፍቃል? ያላዩት አገር ካለሆነ በስተቀር?  ·        ምክንያታዊ ጥያቄ በትህትና … ግን የግድ መልስ ሊሰጥበት የሚገባ።    አንድ ቃለ ምልልስ አሁን አዳመጥኩኝ በናሆ ቲቪ። በግዳጅ ጊዜ ብዙ ፈተና ስላለ አብዛኛውን ጉዳይ እንደማንኛው ወታደራዊ ሥርዓት አዬሁት። እርግጥ የሚያሳዝኑ ነገሮች መኖራቸውን ሳስብ የድምጽ አልባዎቹ የኢትዮጵያ እናቶች ዕንባ ይቆም ዘንድ ፈጣሪ ይህን አዲስ ሰውኛ ዘመን ስላመጣ ተመስገን ማለቴ የዘወትር ግዳጄ ይሆናል። በሌላ በኩል ሃላፊነት እና ተጠያቂነት በዬትኛውም ደረጃ መቀበል እና መፈጸም ደግሞ የነገን የኢትዮጵያ መሪ የመሆን ዕድል ቢገጥም ብሎ