ልጥፎች

የሳጅን በረከት ስምዖን እና የሳጅን ታደሰ ካሳ የዋስ መብት ጥየቃ እና የቦታ ምርጫ ፍርድ ቤቱ እንዳልተቀበለው ተደመጠ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ብራቦ ! የባህርዳር እና የአካባቢው ፍርድ ቤት። „የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል፤ እግዚአብሄር ግን አካሄዱን ያቃናለታል።“ ምሳሌ ፲፮ ቁጥር ፱ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie  ከእመ ዝምታ - ሲዊዘርላንድ 25.01.2018 ·        መነሻ። አሁን የዋልታ ቴሌቪዢን እንደዘገበው የሳጅን በረከት ስምዖን እና የሳጅን ታደሰ ካሳ የዋስ መብት ጥያቃ እና የቦታ ምርጫ ፍርድ ቤቱ እንዳልተቀበለው ተደመጠ። እኛም እልል አለን። ሐሤትም አደረግን። ቀልዱ መቆም እንዳለበተም አበክረን እንገልጻለን! https://www.youtube.com/watch?v=wOycDRy-8eM ዋልታ ቲቪ 17/05/2011 ዓ . ም የቀን 6 ፡ 30 ዜና | Walta TV News 12:30 PM 1/25/2019 ·        ዕይታ። ጤና ይስጥልኝ ውዶቼ እንዴት ናችሁ? ደህና ናችሁ ወይ? ዛሬ አዲስ የብሥራት ሌላ ዜና ደግሞ አለን። ተመስገን ብለን ቀኑን አህዱ እንል ዘንድ የሰማዩ ዳኛ ፈቅዶልናልና። ከፍተኛ ስጋት ነበር በህመም ምክንያት በዋስ የሴራ ቸረቸራ ዋሻው፤ የጥፋት ሥራአስኪአጁ ሳጅን በረከት ስምዖን እና ዋርሳቸው ክንዳቸው - ደጀናቸው አቶ ታደሰ ካሳ /ጥንቅሹ/ ይለቃቃሉ በሚል። ይህ የስጋት ጥያቄ በመጀመሪያው ቀን የተነሳ ነበር። መቼም የአማራ መንግሥት ጅል ካልሆነ በስተቀር አምሱኝ፤ ቅበሩኝ፤ አቃጥሉኝ ካሰኛችሁም ዘልዝሉኝ ካለለ በስተቀር የነቀርሳውን ጭንቅላት ለቆ እንደ ገና በሴራ መርብ እንደ አሳ ለመጠመድ ይወስናል ብዬ አላስብም። ልቡን አውልቆ ልብ አልባ የመኖር ያህል ይሆናል እንዲህ መሰል ኮረኮንቻዊ ዳጣዊ ውሳኔ ከተወሰነ። ቃላትም -

ፕ/አሻግሬ ይግለጡ የኢትዮጵያን ህዝብ ይቅርታ ጠዬቁ፤ የመደመር ፍልስፍናንም ፈቀዱት!

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ቀን የሰጠው ዕውነት ! „ጥበብን አ ውቅ ዘንድ፤  በምድር የሚሆነውንም ድካም አይ ዘንድ ልቤን ሰጠሁ።“ መጽሐፈ መክብብ ፰ ቁጥር ፲፮ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 24.01.2019 የቅኔ ዘጉባኤ። ·        እፍታ።  ጤና ይስጥልኝ የኔዎቹ እንዴት ናችሁ? ደህና ናችሁ ወይ? የአይዋ በረከት ጉዳይ እንዴት ያዛችሁ? ስልኩ የጉድ ነበር አሉ በዬአቅጣጫው አገር ቤትም ውጭ አገርም የእንኳን ደስ አለን። ደስታ ቀላል? ፍትህ በእግሯ ቁማ የሄደችበት ዘመን። ለዚህ ነበር “ ኢትዮጵያዊነት ሱሴ ነውን” ለመቅጨት የወረፋ ሩጫ በነበረበት ወቅት አደብ ግዙ እያልን ስንመክር የነበረው። ጎንደሮች ይህን “የረጋ ወተት ቅቤ ይወጣዋል” ይሉታል። ይኸው ተጋድሏችን ፍሬ አፈራ እንዲህ ...  አሁንም ቢሆን በላይ በላይ የቤት ሥራውን ከመደርደር ልባሞች ስለያዙት አደብ እንላለን ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ፤ ይህንም ጎንደሮች “የፊት የፊቱን ይላል ጓያ ነቃይ” ይሉታል። ግን ጓያን ታወቁታላችሁን? ጎንደር ደንቢያ አካባቢ የሚበቅል የጥራጥሬ ዘር ዓይነት ነው፤ እንደ ሽንብራ ይቃጣዋል … የጓያ ሰባራም የሚባል አለ፤ ሽፋኑ ለጤና አይመረጠም፤ ብቻ ዘሩ እንደ አንዱ ነው ልክ የቋንቋ ዘርፍ የሴም - የካም - የኩሽ እንደሚባለው ዓይነት … ·        ጠብታ። ለ4 ሳምንታት የጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ቃለ ምልልስ ሲያሸን ባጅቶ ዛሬ አጠናቋል። የአውነት ነው ማሸት የሚለውን ነገር የተጠቀምኩት። ልቤ ተንጠልጥሎ ነው የሰነበ ተ ው። ክፍል አንድ አነሰች እንደገና ሳምንት ጠበቅን፤ ክፍል ሁለተም እንዲሁ ... የናፍቁት ነገር ቀርቦ ሲርቅ የደረሰበት ያውቀዋል ...  ብቻ ድምጣቸውን