ልጥፎች

የኢትዮጵያ በሽታ (ከጸሐፊ አቶ መስፍን ማሞ ተሰማ)

 እንኳን ደህና መጡልኝ።  የኢትዮጵያ በሽታ መስፍን ማሞ ተሰማ ሠላም ለናንተ ይሁን! እንግዲህ ምን ይሻላል? ኢትዮጵያ ውስጥ ሁሉም አጥሩን /ክልሉን እያጠበቀ አትድረሱብኝ ማለቱ ብቻ ሳይሆን እዛው ተወልደውና ከብደው ቤተሰብና ንብረት አፍርተው ለዘመናት የኖሩትንም ከደርቡሽ ወይም ከጣልያን የመጡ ይመስል - ወራሪ፤ መጤ፤ ሰፋሪ - እየተባሉ ማቄን ጨርቄን ሳይሉ በአንድ ጀንበር ከነ እንቦቃቅላ ህፃናት ጭምር <የመሬት ባለቤት ነን> ባዮች (ክልላዊ መንግሥታትና ራስ ገዝ ቡድኖች) በግፍ ሲያባርሩና ሲገድሉ <ለተፈናቃይ ሀገር በቀል ስደተኞች> በወቅቱና በተገቢው ሁኔታ የሚደርስላቸውም ሆነ በተግባር የሚቆረቆርላቸው <መንግሥት> አለመኖር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተባባሰ መሄዱ እጅግ አስጨናቂ ክስተት ሆኗል። <ባለ መሬት ነን> ባዮቹንም ሃይ የሚል የመንግሥት ሃላፊ የለም። እንደውም በግፍና ያለ ህግ የተፈናቀሉትን <ለኛ ፖለቲካ በሚጠቅም መልኩ አስፍረናቸዋል> ያሉ <እንደ ሃይማኖት እናምናቸው የጀመርናቸው የለውጡ <ፊታውራሪዎች ኢትዮጵያዊ መሪዎች> ሲናገሩ ከመስማትና ከማየት በላይ ለሰማይም ለመሬትም የከበደ በደልና ሀጢያት ከቶ ከወዴት ሀገር አለ? ይህ ሁሉ ሰቆቃ የሚፈፀመው ደግሞ የ<ህገ መንግሥት> ሰነድ አይናችን ላይ እያወዛወዙና <ኢትዮጵያዊነት ሱስ ነው> እያሉን መሆኑ ነው። እንግዲህ <ህገ መንግሥቱ> ለዘረኝነትና ለአፓርታይዳውያን መሳሪያነት የቆመ ጠበቃ ነው ብንል ሀሰት ይሆናልን?!    <ብሄር ብሄረሰቦችና ህዝቦች> የሚለው ቅጥ አምባሩ የጠፋና ትርጉሙም ፍንትው ብሎ በማይታወቅ <አብዮታዊ ዲሞክራሲ> ንድፈ ሀሳብ አጥር ማጠር/ክልል

ሰብዕዊነት ሲበጠስ ትዕግስትም ይበጠስ ...

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  „በሰዎችና፡ በመላእክት፡ ልሳን፡ ብናገር፡ ፍቅር፡ ግን፡ ከሌለኝ፡ እንደሚጮኽ፡ ናስ፡   ወይንም፡ እንደሚንሽዋሽ ው ፡ ጽናጽል፡ ሆኜአለሁ። ትንቢትም፡ ቢኖረኝ ፥   ምሥጢርን፡ ሁሉና፡ እውቀትን፡ ሁሉ፡ ባውቅ፡ ተራሮችንም፡ እስካፈልስ፡ ድረስ፡ እምነት፡ ሁሉ፡ ቢኖረኝ፡ ፍቅር፡ ግን፡ ከሌለኝ፡ ከንቱ፡ ነኝ። ድሆችንም፡ ልመግብ፡ ያለኝን፡ ሁሉ፡ ባካፍል፥ ሥጋዬንም፡ ለእሳት፡ መቃጠል፡ አሳልፌ፡ ብሰጥ፡ ፍቅር፡ ግን፡ ከሌለኝ፡ ምንም፡ አይጠቅመኝም። „ ( ዬሐዋርያው ዬቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት ወደ ቆረንቶስ ሰዎች ምዕራፍ ፫) ፕ/ለማ መገረሳ ይማሩበት ዘንድ እንደ አዶልፍ ሂተለር በግሎባሉ ከመወገዛቸው በፊት። ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 08.03.2019 ከእመ ዝምታ።                                                   ቃል የእምነት ዕዳ ነበር! ·        ቁጥር አንድ ለእኛ በጥቁር። ዛሬ ሦስት የህሊና ዳኝነት የኦሮምያ ፕሬዚዳንት እና የ ኢትዮጵያ ጠ/ሚር ለማ መገርሳ ይሰጡበት ዘንድ ሦስት ጉዳዮችን ነው እማነሳው። ሦስቱም ተወራራሽ ናቸው።  የኢትዮጵያን መንፈስ ሃይልነት እና 21ኛው ምዕተ ዓመትን ጭንቅ ስለሚለው ሰብዕዊነት እና ተፈጥሯዊነት። የመጀመሪያው ዛሬ „የኔ የነፃነት ቀን #MyFreedomDay “ ነው። በዚህ ቀን 40 ሚሊዮን የዓለም ህዝብ በዘመናዊ ባርነት እንደሚገኝ፤ ከከእነዚህ 40 ሚሊዬን ውስጥም አብዛኞቹ ሴቶች እና ህፃናት እንደሆኑ፤ የሴቶች ደግሞ በመቶኛ ደረጃው ሲለካ 71% ስለመሆኑ የሲኤን ኤን ዘገባ ይገልጣል። ኢትዮ