ልጥፎች

የሰኔሉ መደመር። የቹቻቸው መደመር!

ምስል
ነፍስ ይማር … „ኃጢያትን እንደ ውኃ የሚጠጣ ሰው ምንኛ ያንስ?“  መጽሐፈ እዮብ ፲፭ ቁጥር ፲፮ ከሥርጉተ ሥላሴ Sergute Selassie 23.06.2019 ነፍስ ይማር ለሜ/ጄ ብርኃኑ ጁላ የጦር ኃይሎች ጠ/ አዛዥነት የሥልጣነ ሹመት እና ለጃዋራዊው የጢቾ ባላባት ለአቶ  ንጉሱ ጥላሁን የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳደር ፕሬዚዳንትነት ሲባል መስዋዕትነት ለከፈሉት ለዶር አንባቸው መኮነን እና ለጄ/ ሳህረ መኮነን፤ በተጨማሪም ለአቶ እዘዝ ዋዜ ህልፈት።  እጬጌውን ሂደት ታሪክን ይፍረደው፤ ነፍሳቸውን አርያም ገነት ፈጣሪ ያስገባልን። ለኦነጋውያኑ የምንፈስ ልዕልና ሲባል ለተገበሩት ወገኖቻችን። አሜን! ኩዴታ ነው ካለ የ ኢትዮጵያ መንግሥት ኩዴታውን ያካሄዱት እንሱው እራሳቸው ነፍሳቸው ለጊዜው ምድር ላይ ያሉት ይሆናሉ ... ፎቶውንም ይናገራል። ጠርዝ ላይ ኩዴታ ተካሂዶ አያውቅም። የ አዲስ አባባው ግር ግር ቁሮ ነው ...መለበጫ መስትሽ። ለኦነጋውያኑ የድል ዕለት ብቻ ሳይሆን ለግባቸው አንድ ትልቅ የመገናኛ ድልድይ እርካብ ነው። እነሱ ባቀዱት ልክ አትርፈዋል። ለካቴና ራት እንዲሆኑ ለተፈለጉት ለብ/ጄኒራል አሳምነውና ጽጌ እና ለጓዶቻቸው ደግሞ ጽናቱን ብርታቱን ይስጣቸው። ይህ ሁለት ዓላማ አለው። ህወሃትን ለማስደስትና ልቡ ትንሽ ቢራራ ተብሎ ነው። ተራ በተራ ግን ለአንሳ ሥጋ እዬሰጡ ወደ ማረጃው እንደሚወሰደው ሁሉም ይደርሰዋል የጊዜ ጉዳይ ነው።  ሌላው ግን ቀደም ብዬ እንደገለጽኩት ከተመረጡ ጀምሮ ሥራቸው አጀንዳቸው የአማራ ብሄርተኝነትን ማጠውልግ እና መቅበር ለሆነው አብይወለማ መንገድ ጥሩ ባይታሚን ነው።  የአማራን ቅስም ለመሰበር፤ ጃዋረዊው የጢቾ ባላባት አቶ ንጉሡ ጥላሁን እንዳሻቸው እንዲፏልሉ … ምቹ

አባ ትርጉም ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ትርሲተ ትውፊት ነው።

ምስል

Chapter Five Love Nature Perinciple Delegations, Part Ten

ምስል

የሶማሊ ፖለቲካ ከዳር ወደማዕከል ፖለቲካ እንዴት ይምጣ?

ምስል

መጽሐፍቶቼ የህሊና ልጆቼ፤ ነፃነቴም ናቸው።

ምስል

መጸሐፍቶቼ ልጆቼም ነፃነቶቼም ናቸው!

ምስል
"የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል፤ እግዚአብሔር ግን አካሄዱን ያቃናለታል" መጽሐፈ ምሳሌ ፲፮ ቁጥር፱ ተስፋ ይመጣል ተስፋም ይሄዳል ተስፋም ያነጉዳል  ተስፋም ይክሳል ... አንድ ቀን ... ይጠበቃል!  እንኳን በደህና መጡልኝ  መጸሐፍቶቼ ልጆቼም ነፃነቶቼም ናቸው! ልጆችን መንከባከብ ደግሞ የማህበረሰቡ ተግባር ነው። ተስፋችንም በፖለቲካ ሊሂቃኑ ሳይሆን  በማህበረሰባችን ብቻ ነው! v እፍታ። የኔዎቹ የኔታዎቼ እንዴት ናችሁ የአገሬ ልጆች? ደህና ናችሁ ወይ? ማህበረሰባችን በዬአካባቢው በመንፈስ የታሠሩትን ልጆቹን ማስፈታት ይኖርበታል። ስደት የምንኖረው ባለመክሊት ልጆቹም በስውር ካቴና ነው የባጀነው ውጭ አገር። አብሶ አማራነት ቀራንዮ ነው ። ማህበረሰባችንም እራሱን በሽንገላ ሳይስከበብ ነጥሮ መውጣት ይኖርበታል።  ስለሆነም ለድጋሚ ዕስርም ራሱን ማሰናዳት እንደሌለበት አበክሬ አስገነዝባለሁኝ። ታገሽነቱ በተግባር ይመሳጠር። አሁን ያለው የአገር ውስጥም የውጭ ጭቆና ዓይነት እና ስልትና የጭካኔ ተመክሮ የጫጉላ ሽርሽር እንዴት ሁለቱን አቀናጅቶ ጭቆናን ሉላዊ በማድረግ ንቁ፤ ትጉህ ኢትዮጵውያንን በሁሉም አቅጣጫ ማፈን እና ሰላ ማቸውን ማስጣት ይቻላል ነው ምክክሩ። ይህ ስለላ እሰከ አውሮፓ ህብረትም ይዘልቃል።   ውሉም ጋብቻውም ይኼው ነው። ሞጋች ማህበረሰብ አይፈለግም። ግን ስንቱን አግልለው፤ ስንቱን ከጫዋታ ውጭ አድርገው እንደሚዘልቁት ወፊቱ ትጠዬቅ። ግሎባላይዜሽኑን በኢጎ አፍነው ማስቀረት ከቻሉ ይሞክሩት። ጥቂት ሰዎች ህይወታቸውን ሊያጡ ይችላሉ ... ግን እልፎችን ያፈራሉ ...  ስለሆነም የአፈና እጩን  እንደ መነሻ ከቁምነገር ወስዶ