ልጥፎች

ርህርህና ተሰደደ። እግዚአብሄርም አለቀሰ።

ምስል
እንኳን ወደ ቀንበጥ ብሎግ በሰላም መጡልኝ። እርህርህና ተሰደደ። እግዚአብሄርም አለቀሰ ። „በምድር ላይ የሰው ህይወት ብርቱ ሰልፍ አይደለምን?“ (መጽሐፈ ኢዮብ ምዕራፍ 7 ቁጥር 1) ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie ከጭምቷ©ሲዊዘርላንድ 10.01.2020 እንዴት ናችሁ ቅኔዎቹ የአገሬ ልጆች ? ደህና ናችሁ ወይ? የኢትዮጵያ ፖለቲካ የከረባት እና የገበርዲን ብቻ በመሆኑ ስሞግት ኖርኩኝ። ደጉ ዘሃበሻም፤ ደጉ ሳተናውም ፈቃዳቸውን አልነሱኝም። በራሴ ግራቀኝ ሚዲያም በጸጋዬ ድህረ ገጽ እና ጸጋዬ ራዲዮም በኽረ አጀንዳ ነበር። በሌላ በኩልም በአገረ ኢትዮጵያ ዕንባ ሲበረታ፤ የዕንባ ቅልቅል ሲ ገ ን የድምጽ አልባዎችን የኢትዮጵያ እናቶች ዕንባ አድምጡልን፤ እባካችሁ እርዱን እያልኩ በዬደጁ ስባትልም ምክንያት አድርጌ አቀረብ የነበረው የሴቶች አቅም ዕውቅና አለመሰጠቱ ነው የኢትዮጵያን ችግሩን ያበራከተው፤ ሴቶችም ባለቤት ያጡበት መሰረታዊ አመክንዮ ሴት ወሳኝ ሊሂቃን ወደፊት ባለመምጣቸው ነው እል ነበር። ሴቶች በክህሎታቸው ብቃት ሥርዓቱን የመ ግ ራት፣ የመለወጥ አቅም አላቸው፤ ዕድሉን ካገኙ ሴቶች በጸጋቸው ጸጋ አትራፊ የርህርህና ማህንዲስ የመሆን ተስፋ ይኖራዋል ነበር ሙግቴ። ጠሚር አብይ አህመድ ወደ ሥልጣን ሲመጡ ሴቶችን ወደፊት አመጡ ብዬ ደስ አለኝ። ከቀደመው ሰብዕናቸው ተነስቼም ተስፋ ነበረኝ። ብዙም ጽፌበት ነበር። ያን ስለምን እንዳደረጉት አሁን አሁን የራሱ ዕድምታ እንዳለው እዬገባኝም ነው፤ ያው የወደቀውን ኢህዴግ የግንባራቸውን ሥም ለማደስ ነው የተጠቀሙበት። አሁን ሙሽራው ኢህዲግ ነው ያለው። የሆነ ሆኖ በዛን ጊዜ እኔ ብቻ ሳልሆን ዓለም

50በ60 ያረጠ ፖለቲካ።

ምስል
እንኳን ወደ ቀንበጥ ብሎግ በሰላም መጡልኝ።  „ ለሰዎች ትታዩ ዘንድ ምጽዋታችሁን     በፊታቸው እንዳታደረጉ ተጠንቀቁ። “ ( የማቴዎስ ወንጌል ምእራፍ ፮ ቁጥር ፩ ) 50 በ 60 ያረጠ ፖለቲካ። ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ 06.01.2020 ·         እፍታ። ወይ ጉድ ሦስት ዜሮ እኛን ቁጭ አደርገው ወደ 20 ተሸጋገሩ። ግርም ይላል። ከመቼው 2020 እንደ ተደረሰ። ግን ቅኔዎቹ የአገሬ ልጆች እንዴት ናችሁ? የትውልድ የሃሳብ ብከነት አጀንዳችን ቢሆን ምን ትላላችሁ? ትህትናዊ አክብሮት፤ ትህትናዊ አድማጭነት፤ ትህትናዊ ህዝባዊ ፍቅር፤ ትህትናዊ አስተዳደር ቤተ - መንግሥት ላይ ይተጋጋጠ እዬሆነ ነው። ይትብኃል ሱባኤ ላይ ነው። ቀኑ ይመለ ስ ለት ዘንድ አቤት እያለ ነው ወደ እዮር።  ትህትና ግዞት ላይ ሆኖ በዚህ ፈንታ ፉከራ፤ መታበይ፤ ማን አለብኝነት፤ ደንታ ቢስነት፤ ግዴለሽነትን፤ ጉድለተ - ኃላፊነት የሚያውጁ ሥንኛት፤ ቃላት ቁሙ ተሰቀሉ እያሉን ነው። „ቃል ይተክላል ይነቅላል“ የተባለው ከተከላው ነቀላው ማዘንበሉን እያስተዋልኩ ነው። ሁሉን ነገር ሳልጠራጠር እንደሚቀበል ቅን አንድ ኢትዮጵያዊ ዜጋ በማደምጣቸው ነቃይ ቃላት፤ ነቃይ ሥንኛት የትውልዱን ማግሥታዊ ተስፋ ሳስበው ያምጥብኛል። ይቀጭጭብኛል። ዛሬ ለዕርእሴ ተያያዥ እና ተወራራሽ የሆኑ ጉዳዮችን አነሳለሁኝ። ከ ቅኖች የጹሑፌ ታዳሚዎችም ትዕግስታችሁ እንደማይለዬኝም አስባለሁኝ። ወቀሳዬን እምልክላቸውም ቢሆኑም ያተርፉበታል እንጂ አይከስሩ በ ትም። ለእነሱ የማይታያቸው ለእሷ ታይቷት ይሆናል ብለው በቅንነት ቢያስቡ ትወልድን ከብ ክ ነት መታደግ ይቻላል። ገደል አፋፍ ያለን