ልጥፎች

ሙሽራ ዜና ከሙሽሪት ተዋናይት ሃና የሖንስ።

ምስል
እንኳን ወደ ቀንበጥ ብሎግ በሰላም መጡልኝ። ሙሽራ ዜና ከሙሽሪት ተዋናይት ሃና የሖንስ። „አቤቱ በአንተ ታምኛለሁና ጠብቀኝ።“ (መዝሙር 15 ቁጥር 1) ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 17.01.2020 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ ·         እ ፍታ። ቅኔዎቹ የአገሬ ልጆች እንዴት ናችሁ? ደህና ናችሁ ወይ? አንድ ያልተለመደ ድንገቴ ብሥራት ገጠመኝ እና ዜና ቢጤ ላቀርብ ፈልግኩኝ። ባልደራስ ለኢትዮጵያ ሙሽራም ቤተኛው ሆነለት። ታድሎ! በጥልቀቱ ሲታይ ጣና ዘገሊላ - አስተርዬ አይታያችሁምን? ድንቅነት በህብርነት! ·         ባ ልደራስ ለኢትዮጵያ ሙሽራዊ ረድኤት ቀረበው። „ጥበብ ቤቷን ሰራች፤ ሰባት ምሰሶም አቆመች።“ ሙሽርነት እንዲህ የህዝብ ወገንትኝነት ሲታከልበት ያማራል ይሰምራል። ያበራል ያስተምራል። ቅኔያዊነት ያፈካል። እኛዊነት ያሰብላል። እንዲህ ዓይነት ህብሬነት ትውልድን ከብክነት ያተርፋል። በዚህ ውሳኔ እናታዊነትን አይቸበታለሁኝ። እናትነት እንዲህ ነው ይራራል። እናትነት እንዲህ ነው መከራን ይደፍራል። እናትነት እንዲህ ነው መስቀልን ይሸከማል። እናትነት እንዲህ ነው በመሆን ያምርበታል። እናት እንዲህ ናት ለቸገራቸው ፈጥና ደራሽ። ፈውስ! ውድ እህቴ ተዋናይት እና „የእንተዋወቃለን ወይ?“ የቴልቪዥን ፕሮግራም አዘጋጅ ወ/ሮ ሃና የሖንስ ጋብቻውን የአብርኃምና የሳራ ይሆንላችሁ ዘንድ ከዚህ ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ አንዲት ባተሌ እህትሽ ተስፋዋን እንሆ ላከችልሽ። ውሳኔሽ ከአእምሮዬ በላይ ሆነ።   እንደምን አድርጌስ ልተርጉምሽ? እንደምንስ አድርጌ ላመሳጥርሽ? የዕውነት ከበደኝ። ተስፋ ባጣንበት ወቅት አዲስ የፈካ ቀን ፈቀድሽልን። አንቺም፤ ትዳርሽም፤ ቤተሰቦችሽም የተባ

ባልደራስ ለኢትዮጵያ።

ምስል
እንኳን ወደ ቀንበጥ ብሎግ በሰላም መጡልኝ። ባልደራስ ለኢትዮጵያ እንደ አባት አደሩ ሰንበት ቅኔ ዘረፈለት። „አሁንም ልጆቼ ሆይ ስሙኝ ካፌ ቃል አትራቁ።“   (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ 5 ቁጥር 7) ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 15.01.2020 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ·         እፍታ። እንዲህ በአጭር ጊዜ በ ባልደራስ ለኢትዮጵያ ጉዳይ እመለሳለሁ ብዬ አላስብኩም ነበር። ዘለግ ያለ ሃሳቤን ስለገለጽኩኝ። ብቻ አዎን ብቻ በኽረ አጀንዳችን ይሆን ዘንድ አቅሙን በበለጠ፤ በመሰመረ ሁኔታ ገንቡለት ተባልን፤ ጥበብ ያነሳቸው ፍጥረቶች እነ ማህበረ - ኦነጋውያን። ስለሆነም ደግመህ ናብኝ ማንጠግቦህ ተበላ! እና ብራና እና ቀለም ተመሳጠሩ።  የህልውና ተጋድሎ እንዲህም መራራ ነው። እንዲህም በዬፌርማታው ቀጠሮ የሚሰጥበት አይደለም። ተግ! እስኪ በል ማለት አይቻልም። ቆራጥ ውሳኔ የሚሰጠው እረኛ ያስፈልገዋል። አዲስ አበቤ ሆይ! እንደ ተመኘሁልህ ቀንቶኃ። አይዞህ ባይ ማግኘትህ ን ዕሴትህ አድርገው። ·         በር።    እንዴት ናችሁ ቅኔዎቹ ተዋጥን እኮ በኦነጋውያን የድንገቴ ዝብርቅ ተውኔት። ድብልቅልቅ ያደርጉታል ሁለመናውን። የሰከነውን አዬር እራሱ ይቀኑበታል። ቀናተኛ ናቸው። የረጋውን አውደ ምህረት ቀይጠው ቀወጡት። ሱናሜ ነው የኦነጋውያን ቅይጡ ቅንጡ ንጠት ። ከቶ ተግባባን ይሆን? እኔ ለረጅም ጊዜ ስጽፍበት የባጀሁትን በቅርቡ ለዘሃበሻ ልኬለት አውጥቶት ነበር። ሊንኩን ከሥር እለጥፋለሁኝ። ጉዳዩ የፈረቃም፤ የተረኝነትም አይደለም ከዛ ያለፈ ነው ብዬ ነበር። አምቀው፤ አሽገው አጥረው ይዛዋታል ልዕልት ኢትዮጵያን በቃላት ጅዶ ከሽነው። የችግሩን የውሃ ልኩን ሳታውቅ ትግል