ልጥፎች

የጎማ ካራ

ምስል
  እንኳን ወደ ከበቡሽ ልሳነወርቅ ብሎግ በሰላም መጡልኝ።   ዳጥ በ ~~~ ቁልቁለት ገደላገደል ~~~ በ አቀበት። ኮረኮንች ~~~~ በ ሸካራ ለማልካምነት ፈጽሞ የማይራራ። የእኛ አይደለም ልቡ ነው የጎማ ካራ የጨለማው ባለ ግራጫ ባለዳንኪራ። ጭጎጎት የበቀል የከረፋ በቂም ጨጓራ የጥነት የውድመት የጢሳጢስ አውራ።   " የቤትህ ቅናት በላኝ። "   19.21 ሥርጉተ © ሥላሴ Sergute©Selassie 22/07/2022  

አንሰበርም አንሰበርም!

ምስል
እ ንኳን ወደ ከበቡሽ ልሳነወርቅ ሚዲያ በ ሰ ላም መጡልኝ።   # አ ንሰበርም አንሰበርም ! " የቤትህ ቅናት በላኝ። "   ከቤቴ ከእኔ ጋር የዘለቁ ቅን መስካሪወች አሉ። ቀበርናት ስትሉ የሚንፎለፈለው አቅም በዚህ በሦስት ዓመት ፌስቡክ ላይ ተከሰተና ድንግርግራችሁ ወጣ። ስታሳዝኑ። እንደ እኛ ዝልኝ ሁኑልኝ የገማ መንገድ ነው። እዛው ተጨፋፈቁበት። ወይ ቀልድ። ማህበረ ኦነግን የትናንቱ ውሎዬ ምን አፈራገጣቸው ? እኔ ኦኮ በሙሉ አቅሜ ሠርቼ አላውቅም። ምን እንደ ሠራችሁ እናንተም ታውቁታላችሁ፣ የላይኛውም ያውቃል። ገዳ ለእኔ ሥርዓት ሊያስተምረኝ ? ለመሆኑ እንደ እኔ አክብሮ የሚሞግት አለን ? ከእኔ ፔጅ ላይ የታዳሚዬ ስድብ፣ግልምጫ፣ ውርጅብኝ ገጥሞት ያውቃልን ? ምክንያት እኔ እምሠራው ለትውልድ ነው። ለትውልድ ስሰራ አክሰሱ ላላቸው ልጆችም ተጠንቅቄ ነው። አንተ እና አንቺ እያሉ የሚዘልፋትን ሚዲያወች አላዳምጣቸውም። ከቤታቸውም አልገባም። ስድብ ዕውቀት ስላልሆነ፣ ዘለፋ ልቅና ስላልሆነ። እነሱም ወደው አይመስለኝም ከልክ ያለፈው ጭካኔ ስለ አንገሸገሻቸው ይሆናል። ስለዚህ በዝምታ ሁኜ የራሴን የሚዲያ አክሰስ ግን በራሴ ልክ አክብሬ አስከብሬ እሰራለሁኝ። ከእኔ ፔጅ አንተ ብዬ የሞገትኩት፣ አንቺ ብዬ የሞገትኩት የለም። እንኳንስ ባለስልጣናት የቤቴን ታዳሚወች እራሱ በጓዳ መጥተው አንቺ፣ አንተ በይን ካላሉኝ በስተቀር እርስወ ነው እምለው። ለእኔ ሲል ስዩም ወሮ፣ ወት አይደለሁም ስላ