ልጥፎች

ክፍል አራት ርትህ።

ምስል
ርትህ። ክፍል አራት። ከሥርጉተ © ሥላሴ 01.06.2018 (ከመንኩሲያዋ ሲዊዘርላንድ።) „የሚምሩ ብብፁዓን ናቸው ይማራሉ እና“ (የማቴወስ ወንጌል ምዕራፍ ፭ ቁጥር ፯) ·        መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=_WVc5bXyb5c ጠ / ሚ ዶ / ር አብይ አህመድ ከአፋር ህዝብ ጋር ያደረጉት ሙሉ ውይይት PM Dr Abiy Ahmed discusses with the people of Afar ·        የወግ ገበታ። ውዶቼ ቀደም ሲል የነሳ ኋ ዋቸው ከክፍል አንድ እስከ ሦስት ድረስ ለመነሻ መዳረሻ የሚሆኑትን ብቻ ስለነበር ሊንኩ አለጠፍኩትም ነበር። አሁን በዚህ በክፍል አራት የምናዬው ጠ/ ሚር አብይ አህመድ ሠመራ በነበረው ጉባኤ ላይ የሰጡትን መልስ አስኳል ጉዳዮችን ማዬት ስለሚያስፈልግ ነው። በዚህ ክፍል እስከ መግቢያዋ ላይ ያለችውን ጥላቻን ብቻን ማዬት ብንችል ብያለሁኝ አሁን። እንዳይበዛ እንዲሁም አሰልቺም እንዳይሆን። „ሰው ጠልተህ መተኛት አትችልም። ሌሊቱን ሰውዬው በሌለበት ስትቃጠል ነው የምታድረው። እሱ አያይህም። ያለህበትን ሁኔታ አያውቅም። አንተ ግን ስትቃጠል ታድራለህ። ከዚህ ውጪ መወጣት አለበት። ሰውን ለመጥላት መሮጥ ነገርን ለማሰብ  አዕምሮአችን ማበላሸት የለብንም! ጊዜያችን ማጥፋት የለብንም! እኛ ምን እንደርጋለን? ሰው እንወዳለን! ሰው እናቀርባለን! እስከተቻለን ድረስ ሰውን እንረዳለን። ነገር ግን የሚጠሉን ሰዎች እንደሚኖሩ እናውቃለን። ዓለም እንዲህ ስለሆነች። ሰዎች ሲጠሉህ አንተም ቁልቁል ተመልሰህ ጥላቻ ውስጥ ከገባህ በእነሱ ሜዳ ውስጥ ገብተህ እዬተጫወትክ ነው ማለት ነው። የጦር ሜዳው

ክፍል ሦስት - ርትህ።

ምስል
ርትህ። ርት ክፍል ሦስት። ከሥርጉተ © ሥላሴ 30.06.2018  (ከመንኩሲያዋ ሲዊዘርላንድ።) „በመንፈስ ደሃ የሆኑ ሰዎች ብጹዓን ናቸው፤      መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና“ (የማቴወስ ወንጌል ምዕራፍ ፭ ቁጥር ፫) ·        የ እኔ ክብረቶቼ ውዶቼ … ቀደም ባለው ጊዜ ቅኑ እና ደጉ ሳተናው ብዙ ደንበኛ ስላለው አበዛበታለሁ በማለት የምዘላቸው ብዙ ጉዳዮች ነበሩ። አሁን በራሴ ብሎግ ላይ ስለምሰራ አባዛለሁኝ የሚል ሰቀቀን ስለሌበኝ በሙሉ አቅሜ እሰራለሁኝ ብያለሁኝ ከፈጣሪ ጋር። የምዋሳው ሆነ ከሌላ የምጠብቀው የብዕር የህሊና ምርት የግብይት ሥርዓት ስሌለበኝም እራሴው የሚሰማኝን እንደ ገባኝ እጠፈዋለሁኝ። ማንዘርዘሪያ ወንፊቱ ደግሞ የእናንተ የመንፈስ አዱኛዎቼ ነው።  ባፈው ሳምንት ለጋዜጠኛ መሳይ መከነን „አንዳንዶቹ ባይደመሩስ“ በሚል  መጣጥፍ ላይ ስሞግት እኔ ስለማጠሪያ፤ ማንዘርዘሪያ ወንፊት ዓይነ ጠባቦች የመደመርን ፍልስፍና ያሰተነጋዱበት ጠንጋር ዕሳቤ፤ መደመርንም እኛ እንምራው ዓይነት ጉዞ ስጥፍ ተናግሬ ነበር። ዛሬ በሠመራው ጉባኤ ይኸውኑን ጠ/ ሚሩ ሲናገሩት ሰማሁኝ። ቅንነት ካለ ሳትነጋገሩ፤ ሳትተዋወቁ፤  አንዱ አፍሪካ ሌላው አውሮፓ ላይ ሆኖ አንድ በሚያደርገው የሃስብ ሃዲድ ትገናኛለችሁ ካለ ድርጅታዊ ሥር ማለት ነው። ካለ ካድሬያዊ ፕሮፖጋንዲስት ወይንም የፕሮቶኮል ጣጣ ምንጣጣ ማለት ነው። መደመር አብሮ መደመር ነገር ግን ቅሬት አካሎች ሳንክን ፈጣሪ ከሆኑ በማጣሪያው ተግባር ይጣለላሉ ማለት ነው።  የሆነ ሆኖ አሁን ወሳኝ የሆኑ ጉዳዮችን ከሥር ከሥር መሥራት የሚያሳቅቀኝ ነገር ዛሬ ላይ የለበትም። ስለዚህም የአፋርን ዕድምታ ሠመራን መነሻ በማድረግ ምእራፍ አንድ እና ሁለትን ጽፌያለሁኝ የጉዞ

ርትህ ክፍል ሁለት።

ምስል
ርትህ። ክፍል ሁለት። ከሥርጉተ © ሥላሴ 30.06.2018         (ከመንኩሲያዋ ሲዊዘርላንድ።) „ጽድቅን የሚራቡና የሚጠሙ ብጹዕን ናቸው“  (የማቴዎስ ወንጌል ምዕራፍ ፭ ቁጥር ፮) ·       እ ፍታ እንዴት አላችሁልኝ የአገሬ ልጆች? ደህና ናችሁ ወይ? እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ። ዛሬ በርካታ ነገሮች ቢኖሩም ቅድሚያ ሰጥቼ ምልከታዬን ላጋራችሁ የምሻው የአፋሩም የሠመራ ጉባኤ ጥያቄ እና የመልሱን ዕድምታ ነው። እርግጥ ነው ይሄ መቅድም ስለሆነ ተያያዥ ነገሮች ማንሳቱ ግድ ይለኛል። የክልሎች ማሰረጊያም ጉባኤ ስለሆነ። ምክንያቱም የጠ/ ሚር አሜኑ አብይ የመንፈስ ነፍስ እኔን እንደ ገባኝ በሁለመና የተቃኘ ንድፍ አለው። የሠመራው ከክልል አንፃር ማጠቃለያው ነው። ቀጣዩ የተጎዱ የቀደሙ የክ/ አገር ከተሞችን እና በአቻነት የሚታዩት ላይ ቢሆን የሚል እሳቤ አለኝ። ቢሆን ምርጫዬ ነው እንደ ማለት።  ደሴ፤ ጅማ፤ አሰላ፤ መቱ፤ ድሬድዋ፤ ሻሸመኔ፤ ሙያሌ፤ ነቀምት፤ ማርቆስ፤ ደብረታቦር፤ አርባምንጭ፤ ደብረብርሃን እንደዚህ በዓመቱ መርሃ ግብር ቢካተቱ መልካም ነው።  አሁን ደሴዎች ሰሞኑን ከአቶ ገዱ አንዳራጋቸው ጋር ውይይት ነበራቸው፤ ተዜትኛው ምዕተ ዓመት እንዳለች ደሴ ግራ ያጋባል። አሁንም ሜዳ ላይ ነው ጉባኤው የተካሄደው። ይሰቀጥጣል። ·       ክ ብረቶቼ። ክፍል አንድ ላይ ጠ/ ሚር አብይ አህመድ „የዙረት አበዙ“ መንፈስ አባዜም አፋር ላይም ተደምጧል። በክፍል አንድ  የጉዞውን ዓላማው አቅጣጫ በሥርጉተ ግንዛቤ አቅርቤያለሁኝ። ቀጣዩ ደግሞ ምምን እንኳን የኤርትራ እና የደቡብ ሱዳን ገና የቀረ ነገር ቢኖርበትም። የእነሱም ቢሆን ሰሞናቱን ባለ ቅኔው ጠ/ ሚር አሜኑ አብይ