ልጥፎች

ቅኝቴ ነሽ!

ምስል
„እኔ ብናገር ህመሜ አይቀንስም፤  ዝም ብል ከእኔ አይወገድም።“ (መጽሐፈ እዮብ ምዕራፍ ፲፮ ቁጥር ፮) ሥርጉተ© ሥላሴ 28.07.2018 (ከዝምተኛዋ ሲዊዝ) ይህ ፎቶው ያነሳችኝ መምህሬ ናት - የሥነ ጹሁፍ ክፍለ ጊዜ ላይ፤ ለሦስት ተከታታይ ዓመት በሳምንት አንድ ቀን አንድ የስደተኛ መጋዝን ዝግጅት ውስጥ ከነበረው ቡድን ጋር እሰራ ነበርኩኝ፤  ያው በነፃ ማገልገል እግረ መንገድም መማር ስለሆነ። ለመጽሄቱ የመጀመሪያውን የሥነ - ግጥም አምድ ያስጀመርኩት እኔ ነበርኩኝ። ከዛ በኋ ዋላ ነበር መምህሬ እና አለቃዬ  የዓለምን ዕውቅ የሥነ ግጥም ባለቅኔዎች ማሰስ የጀመረቸው።  ሌላው አለቃዬ ሁልጊዜ ስትናገር ሥርጉተ ተማሪ ብቻም አይደለችም ባልደረባዬም ናት ትል ነበር። ብዙ ጌዜ መጋዝኑን እርእስ እኔ እረዳት ነበር፤ ለይ አውቱንም፤ በተጨማሪም ኬኒያ ለሰባዕዊ መብት ጉባኤ የሄደችው ዋና አለቃችን  እኔን የሚያውቅ ሰው አግኝታ ዝርዝር መረጃውን በኢሜል ስትልክላት የነበራት ደስታ ይህ ነው አይባልም። አልናገረም ነበር እኔ ምን እንደነበርኩኝ። መረጃ የሰጣት ወንድሜ ሙሉ ስብዕናዬን እና ተመክሮዬን ነበር። የቅርብ አለቃዬ እና መምህሬ የልጆች ጋዜጠኛ ነበረች። አሁን ሌላ ፕሮጀክት ውስጥ ነው የምትሰራው።  እኔን ወደ ልጆች ራዲዮ አዘጋጅነት እንዳተኩር ያደረገኝም የእሷ ተመክሮም ጭምር ሲሆን ለኢትዮጵያ የነፃነት ትግል ብዙ ደክማለች። መረጃ በማሰባሰብ እረግድ ብቻ ሳይሆን በመሰጠት እረገድም። አብሶ በስብዕዊ መብት ረገጣዎች ጉዳዮች ላይ ሰፊ አትኩሮት አላት። እኔም በብዙ ሁኔታ አግዛኛለች። ቤቷ ስሄድ እንደኛው ባህል አልጋዋን ለቃ እሷ ከታጣፊ አልጋ ተኝታ ታስተናግደኝ ነበር። እሩቅ ግን በሽኝት ሄጄ እምሰራበት ራዲዮ የኢትዮ ኮሚኒቴ ፕሮግራም ስ

የዕለቱ መልክቴ።

ምስል
„መንፈሴ ደከመ ዘመኔ አለቀ፤ መቃብር ተዘጋጅቶልኛል።“ (መፅሐፈ እዮብ ምዕራፍ ፲፯ ቊጥር ፩) ከሥርጉተ ሥላሴ 28.07.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።) የዕለቱ መልክቴ። የኔዎቹ ቅኖቹ ግን ጥቂቶቹ እዚህ ዳምኗል። ተጫጭኖታል። ኢትዮጵያም ደምኖባታል። ነገም ሞት ስለሚጠበቃት። ዜግነት ከደመና አልፎ ጠቁሮበታል፤ ጠባቂ አልባ መሆኑን መስቀል አደበባይ ስላወጀለት። የዲሲውን የሥም፤ የዝና፤ የክብር ይገባኛል ግብግብ ልታደመብት አልፈቀድኩም።  በዚህ ጨለማ ቀን በሚለቀስበት ቀን አልወደውም ለተኖረበት ዝና መውደቅ መነሳቱን። በመከራ ቀን ራስን አጀንዳ እድርርጎ መውጣቱን ያቅለሸልሸኛል። ውሸተኞች መሆናችንም መግለጫው ይሄው ነው። „ነፃነት ነፃነት ነፃነት“ ግን የእውነት ነውን? አልነበረም? ለነፃነት የሚደረገው ተጋድሎ አጠገብህ ያለውን ነፃነቱን ስትጠብቅለት ነው፤ ዘግተህና ቆልፈህ የያዝከውን በሩን ስትከፍትለት ነው። የምታውቀውን ንጥረ ነገር አውጥተህ ስትመሰከርለት ነው። ስለ አንተ ሳይሆን ስሌላው ብቃት ሞግተህ ስትረታለት ነው። ከአንተ የተሻለ ጀግና እና ብቁ ሲመጣ አፍነህ ወይንም አዳነፍነህ በመቅበር ጀግንነት ጸንቶ አይቆምም። ነፃነት ከአንተ በላይ ጀግና መፍጠር ስትችል ነው ታገልኩለት ማለት የምትችለው። ስተትተካ፤ ራሱን የተካ ሲመጣ ደግሞ ሳጥፈራው፤ ሳታገለው አጥፍህ ሳትይዘው ነው ...  ከዚህ አልፈህ ለኢትዮጵያ ህዝብ ተቆርቋሪ ነኝ ብትል የምንታዘብ ሰዎች ስላለን ቢያንስ ዕንባችን ወደ እዬር እንልካለን። ሌላ አቅም ስሌለን ። ከዘመነኛ ጋር ስለተጠጋህ የዘመንክ ሊመስልህ ይችላል፤ ግን ከዘመናኛ ጋር እንድትጠጋ፤ ተቀባይነት እንዲኖረህ ያደረከው ግን ያ በመንፈስህ ያገለልከው የእያንዳንዱ ስደተኛ የ

የአማራ ሊሂቃን የሞት ፍርድ?

ምስል
ይገርማል? ዝንቅንቁ የሰናፍጭ   እና  የጤፍ ፍጭቱ ግብረኛ? „ዋይታ ለማን ነው? ሃዘን ለማን ነው? ጠብ ለማን ነው? ጩኽት ለማን ነው? ያለምክንያት መቁሰል ለማን ነው? የዓይን ቅላት ለማን ነው?“ (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፳፫ ቁጥር ፳፱) ከሥርጉተ© ሥላሴ 27.08.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።) የኔዎቹ ዛሬ በመደዳ ነው የምሄድበት፤ አሜሪካኖች ማን ይገኝ አይገኝ ሙግት ላይ ናቸው ከኢንባሲው ጋር፤ እኔ ደግሞ አገር ቤት ያለው ጭጋጋዊ ጉሙ ያስጨንቀኛል፤ እንቅልፍ ነስቶኛል። አዬር ላይ ራሱ አውሮፕላኑ ከማረፉ በፊት ምን ይገጥመው ባይ ነኝ።  የገረመኝ በዶር አብይ አህመድ ሰብዕና ዲሲዎች ተደናግጠዋል፤ ይገርማኛል ሰው እኮ ጥሩ ልሁን ቢል በአንድ ጊዜ አይችልም። ሰብዕናው አብሮ ካልተፈጠረ። ለነገሩ ተራራ ሲያ ለባጀ ሊደንቅ ይችል ይሆናል …    ግን ወገኖቼ የት ነበሩ? የመረጃ ምንጫቸው በቃ ሚደያው ያደማባቸው ማህበርተኛ ብቻ ነበሩን? አንድ መሪ ሲመጣ ግድ የሚሉ ነገሮች ይኖራሉ። ወደፊት የመጡ ሰዎችን ማጥናት እኮ የዜግነት ግዴታ ነው። የመምርጥ መብት ላይኖር ይችላል፤ ግን በመንፈስ ለመቀበልም ላለመቀበልም ቅድመ ጥናት ማድረግ ይገባል … አብይ ሆነ ለማ ዛሬ አልተፈጠሩም፤ አሜሪካ ስለተገኙም አይደደለም ጥሩ ሰዎች የሆኑት።  … ሰብዕናቸው እና እምነታቸው አስተዳደጋቸው እና ተፈጥሯቸው ይሄው ነው። ራሱ ቡድናቸው የሚመሰጥ ነው። ቡድናቸው ስል የፖለቲካውን ማለቴ ሳይሆን ሃይማኖታዊውን ወይንም የሰውን ህሊና ለበጎነት ለማሳናዳት ያላቸው የትትርና ማህብር ማለቴ ነው። የሆነ ሆኖ … ዛሬን ንዑስ እርስ ላስኬደው ነው … በመደዴው ሞትና የአማራ ሊሂቃን በተቀደ ሁኔታ። … ይግርመኛል የመግለ