ልጥፎች

ቆሞሳት እና ቅናዊ ምዕራፍት!

ምስል
የቆመሱ ፈቃደ ተክለማርያም „ስንብት“ በፈቃዱ  የሰላም ሐዋርያነት   ነው። „የቀደሙት ነብያት ለአባቶቻችሁ እንዲህ ብለው ሰብከዋል፣ --- የሠራዊት ጌታ እግዚአብሄር እንዲህ ይላል፣ --- ከክፉ መንገዳችሁ እና ከክፉ ሥራችሁ ተመለሱ፤ እነርሱ ግን አልሰሙም፤ እኔንም አላደመጡም፤ እንደ እነርሱ አትሁኑ ይላል እግዚአብሄር።“ (ትንቢተ ዘካርያስ ምዕራፍ ፬ ቁጥር ፩) ከሥርጉተ©ሥላሴ 02.08.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።)    v     ልመና። እጅግ የማከብራችሁ የአገሬ ልጆች ትንሽ ለዬት ያለ እድምታ ስለሆነ በጽሞና ትከታተሉት ዘንድ በዘንካት ትሁት መንፈስ እጠይቃችሁ አለሁኝ፤ እኔ ሎሌያችሁ ሥርጉተ ሥላሴ።   v   መካሄጃ። ዛሬ ደግሞ የቀብር ሥርዓት አለ። ማልቀስ ግን አይገባም። ማንባትም አይገባም። ይህን ሳለደርግ፤ ይህ ሳይሆን ሊባልም አይገባም። ይህ ሊሆን ግድ ያለበት እዮራዊ የሚስጢር ዕድምታ ስላለው። የመጨረሻም ቢሆን ስንብቱ ግን እዬራዊ ሥራ አለበት ስለሆነም እባካችሁን ሃዘኑን በልክ አድርጉት። ታላቅ መነኩሴ ነበር። ቆምሶ ኖሮ ነው፤ ቆምሶ ነውም ያለፈው።  የኔዎቹ ግራ አይገባችሁ እገልጠዋለሁኝ የሚሰማኝን። ሰማዕትነትን ዘመኑ ፈቅዶታል። ሁለት ሰማዕታት ሰኔ 16 ቀን፤ በወሩ ሀምሌ 19 ሌላ ሰማዕት፤ የተክልዬ ጊዮርጊስ ለተክልዬ ሌላ የሰማዕትነት ዜና አዲስ አበባ አስተናገደች። ጸጥ ረጭ ብላ የባጀቸው አዲስ አበባ ሁሉንም በዓይነት እያስተናገደች ነው። ተደሞን ለተደሞ ጊዜ ከተሰጠው።   v   ትውስታ። ታስታውሱ ከሆነ ማን ጠ/ ሚር ይሁን በሚለው ላይ የዶር አብይ አህመድ ወደ ፊት መምጣት አስመልከቶ ሰፊ ጫና ነበር። ቀድመው ዶር ለማ መገርሳን የማይደግፉት የነበሩ

ቅዱሱ ሙሴ አብዩ አሜኑ እንሆ ዛሬም ዲያቢሎስን ድል አድርገ!

ምስል
የአብዩ አሜኑ ገድለ ድርሳናት እነሆ ታዬ! ቅዱሱ ሙሴ እንሆ ዛሬም ዲያቢሎስን ድል አድርገ!                    „ ጥብብ ቤቷን ሠራች፤ ሰባቱንም ምሰሶዎች አቆመች።“                  (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፱ ቁጥር ፩) ከሥርጉተ©ሥላሴ 01.07.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ) ·        ከዘመ ናት ህማማት ወደ ሰሞነት ትፍስህት። እንቅልፍ አልተኛሁም። እንዲህ ነኝ እኔ በማንኛውም ወሳኝ ጉዳይ ላይ ስጋተኛ እና ፈሪ ነኝ። ስለሆነም ከመተኛት መዝምሩ ዳዊትን ሳነብ ማደሩን መረጥኩት። ያኖረኝ የልብ አምላክ ዳዊት ቅኔ ነው። የሚገርመው ሰውነቴ ንቁ ነው። እንቅልፉ በኗል። እንሆ ይህም ምኞቴ ተፈጸመ „አድርገህልኛል እና ለዘላለም አምሰግንሃለሁ።“  (መዝሙር ምዕራፍ ፶፩ ቁጥር ፱) https://sergute.blogspot.com/2018/07/blog-post_76.html „አዲስ ቅዱስ ጸበል በመንፈስ ሲፈልቅ የተዋህዶ ተጋድሎው ሊገፋው አይገባም“ የሚል ብፁዕን አበው አገር መግባት አለባቸው፤ መሞት ካለባቸውም ሄደው የሰማዕትነት ጽዋውን ይቀበሉ፤ ይህን የምርቃት ታምራት ሊገፉት አይገባም ብዬ ጽፌ ነበር።  ታዳሚዎቼንም በዬፌስ ቡካችሁ ለጥፉልኝ ብዬ ተማጽኜ ነበር። ምኞቴ እንሆ ተፈጸመ። በስልክም እስከ ንግቱ 9 ሰዓት ድረስ ስወያይ ነበር ቁጭ ብዬ ያድርኩት። መንፈሴን ከተጋራችን ነፍስ ጋር። መወሰን ያልደፈረ መኖርን አይጀምርና። ቅደስት ተዋህዶ በባዕቷ ትውፊት እና ትሩፋቷን ያከበረው እዬራዊ ታምር ጸሎታ የተደመጠው መጋቢት 18 ቀን 2010 ነበር። ቅብዕው ደግሞ የተክልዬ ዕለት ነበር።  ፈጣኑ ሐምሌ ኡራኤል፤ ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ ትክልዬ ጥሪውን እንሆ መልክ አስያዙት። ዛ

ታላቅ የምሥራች ከኤርትራ መንግሥት ተደመጠ!

ምስል
እንሆ በአንድ ወር ውስጥ ፕ/ ኢሳያስ አፈወርቂ የልቤን አደረሱልኝ። አምላኬም ፍላጎቴን አዳመጠ። ተመስገን! „ወዳጅህን ሂድና ተመለስ ነገ እሰጥሃለሁ አትበለው፣ በጎ ነገር ማደረግ ሲቻልህ።“ (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፳፱) ከሥርጉተ©ሥላሴ 01.08.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ።) ·        ሰላምታ። ጤና ይስጥልኝ ፕ/ ኢሳያስ አፈወርቂ እንደምን ሰነበቱ? እነኛ ደስ የሚሉ ፍቅር የሆኑ ቤተሰቦቸዎትስ? እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ። ዛሬ ዘሃበሻ የሚባል ድህረ ገፅ ላይ አንድ መልካም ዜና ሰማሁኝ፤ ቀደም ባለው ጊዜ እኔም አምደኛ ነበርኩኝ። ኤርትራ የሚገኘው ባቶ ዳውድ ኢብሳ ለሚመራው የኦሮሞ ነፃ አውጪ ድርጅት ሁለት አዎንታዊ አማራጭ እንደሰጡት አዳምጫለሁኝ። እጅግ አድርጌ አመሰግነወታለሁኝ። ይህቺ የቡኒነት ወላዊነት የዘመናችን የልባዊነት እኛዊነት ልዩ እዮራዊ ሸልማት ናት። ቀደም ብዬም ምን ያህል መልእክቴ እንደደረሰ ባላውቅም፤ ይህኛው አዲስ የጀመርኩት ብሎግ ስለሆነ ጥቂት ቅኖች ብቻ ስለሆነ የሚታደሙበት ላያገኙት ይችሉ ይሆናል፤ ከኤርትራ መንግሥት በዚህ ስምምነት ከምፈልገው መንፈሳዊ ጉዳይ ትልቁ እና ዋንኛው ማንኛውንም የኤርትራ መንግሥት ያስታጠቀቻቸው የነፃነት አርበኞች ወደ ኢትዮጵያ እንመለሳለን ሲሉ ትጥቅ እንዲያስፈቱ በታላቅ ትህትና ጠይቄ ነበር።  አሁን የልቤን አድርሰውልኛል እጅግ አድርጌ አመሰግነወታለሁኝ። ይህ የኢትዮጵያ ሰላም መሆን ለኤርትራም በ እጅጉ ያስፈልጋታል። ስለዚህ ኤርትራ ለራሷ ሰላም እምትሳሳ ከሆነ ማደረግ የነበረባት ቀዳማዊ እርምጃ ይህ ነበር። ·        ማመሳከሪያ። https://sergute.blogspot.com/2018/07/blog-post_46.html