ልጥፎች

ዕውነት አንቀላፋ በጃዋር ቀያፋ።

ምስል
ውሎሽ? „ሁለት ዓይነት ሚዛን በእግዚአብሄር          ዘንድ አጸያፊ ነው“                 መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፳ ቁጥር ፳፫ ከሥርጉተ©ሥላሴ 20.29.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።                   የስቃይ በረከት የዕንባ ዋናተኛ                   የፍትህ ውሏዋ የት ይሆን መገኛ?                   የጃዋር መ ጋ ኛ ለሽብር አይተኛ።                   ለጃዋር እርካታ የሚሊዮን ዋይታ፤              ለጃዋር ልቅና በመዲናዋ ላይ ንጹሃን ይሰዋ!                   ለጃዋር መታበይ አጀብ ነው ሁካታ ¡                   ለጃዋር ጭካኔ የመንግሥት ትርክታ!                    ለጃዋር ግነቱ ሚዲያ ክርፋቱ፤                    ለጆዋር ቅልቅል የሜጫ ቱማታ።                   ለጆዋር ምርቃና የእልቂት ሀተታ፤                   ለጃዋር ሠራዊት ፋክሊቲው ይዘጋ፤                   ይገዛ ይከመር፤ የሰጋት አለንጋ¡                  ለጆዋር ገረፍታ ጭብጫባ ሲቧካ፤                  ለጆዋር ዕውቅና ያዋጣል ብዥታ።                   ለጃዋር ንግሥና ህግጋት ይመታ¡                   ለጃዋር ዲስኩሩ ሚሊዮን ይምታታ!                   ለጃዋር ንግሥና የግራኝ ትዝታ!                   ለጃዋር ድንፋታ የእልቂት ሽውታ!                     ከጃዋር ሞቅታ የበቀል ገበታ፤            

በግንቦት 7 አይመሃኝ፤ ራሱ የችግሩ ጠላላ ከኦህዴድ ውስጥ ነው።

ምስል
ጮፍራራው ዕብለት። „ወርቅ እና ብዙ ቀይ እንቁ ይገኛል፤ የውቀት ከንፈር ግን የከበረች ጌጥ ናት።“ መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፳ ቁጥር ፲፭ ከሥርጉተ©ሥላሴ  20.09.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ·        መነ ሻ። https://www.youtube.com/watch?v=FH6ngTrfYX4 Ethiopia: ጥቃትና ግጭት የቀሰቀሱ ቡድን አባላት ተይዘዋል ተባለ ዶክተር ነገሪ ሌንጮ፤ እንደምን ያለ ዝልብ መረጃ ነው እኒህ የኦሮሞ ሊሂቅ የሚሰጡት። ምኑ እና ምኑን ነው የሚያገናኙት። ረግረግ። ·        ባጠ ቃላይ፤ እጅግ የሚገረሙ የለበጣ ሰብዕዊ መብት ረገጣዎችን እኛ አይደለነም እመኑን ነው ሳርቅጠሉ ላይ ሶኬት ማይክ ሰክተው የሚነግሩን። የሰኔ 16ቱ የሲቃ ድባባ፤ የቆሞስ ስመኛው በቀለ ራሱን አጠፋ ድራማ፤ ለቀበር የወጣው ህዝብ አንግልት እና እገዳ፤ የመስቀል አደባባይ የካሜራዎች ቀድመው መነሳት እና ሂደቶቹ፤ የሰሜን አሜሪካ ጉዞ ጋር የነበረው ግጥምጥሞሽ፤ የ አቶ ተስፋዬ ጌታቸው ህልፈት፤ ከዛ መልስ የተፈጠረው የተደሞ ሰሞናት ጭጭ ረጭ ያለው የመፈንቅለ መንፈስ ሙከራ የኩዴታ ምልክቶች ሆነው ነገር ግን „የቀን ጅቦት፤ በገንዘብ የተገዙ፤ ቦዘኔዎች፤ የጥፋት ሃይሎች ያሳደነዷቸው“ ጭፍርር ያለ ዕብለት ይደመጣል። አሁንም የሶሞናቱ ጉዳይም እንዲሁ። ምንጩ አንድ ነው። ግን ያ አንድ ነገር ወገን ሆነና እና እንዴት ከችሎት ጋር ይገናኝ። እንዴት ሚዛናዊ ፍትህ ያግኝ? የአቤል ጩኸት የፍትህ ያለህ ይላል። የሰኔ 16 የተከሳሾች የቀጠሮ መራዘም ጉዳይ ምንጩ ይኸው ነው። ምንአልባትም ዋና ወንጀለኞች ቦታ እስኪይዙ ድረስ ሊሆን ይችላል። „ሌባን ሌባ ቢሰርቀው ምን ይበጀው ነበር“ እንደሚበላው ጉዞው

ብልሃት የሌለው ቅላት በግራ ቀኙ ሲፈታተሽ።

ምስል
ተገፊው ማህበረስብ ዛሬም እንደ ትናንቱ ነገም…    „በሚያልፍ ቢዚህ ዓለም የምትኖሩ እናንተም መኳንንቱና ነገሥታቱን በሚገባ ሥራ ጸንተው የኖሩ ከናንተ አስቀድሞ የነበሩ አባቶቻችሁ እንደዚሁ መንግሥተ ሰማያትን እንደ ወረሱ ስማቸውም ለልጅ ልጅ ያማረ  እንደሆነ አሰቧቸው።“ መጽሐፈ መቃብያ ካልዕ ምዕራፍ ፲ ቁጥር ፳፯ „ኃኋ ከሥርጉተ©ሥላሴ 18.09.2018 ከጭምቷ ሲወዘርላንድ። ድሃን ስላስጠጋች ቅድስ ቤተ ክርስትያነችን ስትደፈር። https://www.zehabesha.com/amharic/archives/94354#respond ከሶማሌ ክልል የተፈናቀሉ የአማራ ክልል ተወላጆች በባህርዳር ከተማ ቤተክርስቲያን ደጃፍ በልዩ ሃይል ተደበደቡ https://www.youtube.com/watch?v=8shYma5YbO8 Ethiopia || የትግራይ ልዩ ሃይል አፍኖ እየውሰደ በደል እየፈጸመብን ነው Published on Sep 18, 2018 ·       ለምን? ዶር አብይ አህመድ እስቲ ይቆንጠጡ። „ለምን“ ቃሉ ፍልስፍና፤ ለማወቅ መሻት፤ ለመመርምር መፈልግ፤ ለመፍጠር መነሳሳትን ያመለክታል ... ቃሉ አቅም ይፈጥራል፤ ግርዶሽን ይገፋል፤ ጨለማን ያስወግዳል። „አይ“ ዕውነት ዕብለትን እንዲበቀለው አቅም ይለግሥሳል። ፍቅራዊነት መርሆ ጥላቻን ይበቀላል። ጥላቻን የሚበቀለው የትምህርት ዓይነት ቢኖር ፍቅራዊነት ብቻ ነው። ሥርጉተ ሥላሴ ስታድግ አይደለም ወላጆቿን፤ ሊቀ - ሊቀውንት አያቶቿንም፤ የቀለም መምህራኖቿን „ለምን“ ብላ ትጠይቅ ስለ ነበረ እድገቷም ዕውነትን በመፈለግ ላይ ያተኮረ ነበር። የንግግር ጥበብ መምህሬ ጋሼ አብነት ለምን መምህር ሆነህ ብላኮቦርድ እና ቾክ ትጠላለህ ብ