ልጥፎች

ፈሳሽ ፖለቲካ እና አደጋው። ሻማዋም ኑዛዜ ላይ ናት።

ምስል
ጥምዝምዝ አመክንዮ። „የእግዚአብሄር ቃል እንዲህ ሲል ወደ እኔ መጣ፣--- የሰው ልጅ ሆይ፤ የወይን ግንድ፣ በዱር ዛፎች መካከል ያለ የወይን አረግ ከዛፍ ሁሉ ይልቅ ብልጫው ምንድር ነው?“ ትንቢተ ህዝቅኤል ምዕራፍ ፲፬ ከቁጥር ፲፪ እስከ ፲፫ ከሥርጉተ©ሥላሴ 24.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ·        ጭ ብጥ። መሻገር በአዎንታዊነት ቢሆን ምንኛ መልካም በሆነ። ወንዝ ከላይ ከላይ ሌላ ቦታ ዝናብ ሲጥል በድንገቴ ወንዙ ይሞላ እና ብዙ አደጋ ያስከትላል። ማለትም እዛ አካባቢ ዝናብ ሳይኖር ማለት ነው። የችግሩ ምንጭ ከሌላ በሚነሳ እንደማለት። ሙላቱም ደራሽ ይባላል። ምንልባትም ከሰዎች ተሻጋሪዎች በተጨማሪም የጋማ ከብቶችም ሊኖሩበት ይችላል።  አገር ሰላም ነው ብለው በተለመደው አኳሆን መሻገር ሲጀመሩ ድንገት ዶል ይልና ደራሹ የመጨረሻ ስንብት ይሆናል። የዋና ሙያተኛ የሆነው ግን ምን አልባት ከንፍሮ ጥሬ የሚያወጣው አምላክ ይድን ይሆናል። የኢትዮጵያ የቀውስ መነሻ ውስጣዊ ብቻ ነውን? እእ!የፈሳሽ ፖለቲካ አደጋ ይታዬኛል።  ወደ ቀደመው ጭብጤ ምልሰት ሲሆን አካባቢውን አጥንተው ሰማዩንም አስተውለው ላይ ዘንቧል ብለው የሚያስቡ ጠንቃቆች ግን ከመግባታቸው በፊት ወደ ወንዙ በተረጋጋ ሁኔታ አደብ ስለሚገዙ ብዙም ለአደጋ አይጋለጡም። ደራሽ ሙላቱ ተግ ሲል ሁሉም በነበረው መልክ ሲረጋጋ ሁሉም ወደ ቦታው ሲመለስ ወንዙን አቋርጠው ወደ ቀያቸው ይገሰግሳሉ። ለዚህ ነው አበው „የሚያልፍ ዝናብ አይምታህ“ የሚሉት። ግን ኦዴፓ ይህን አስተውሎታልን? መሪው አገር መሪው አስተዳዳሪው አውራ ፓርቲ እሱ ስለሆነ። አሁን እማያቸው ጉዳዮች እና መጪውን ጊዜ በእጅጉ ያሰስበኛል በ2017 ህዳር ወር ላይ VOA ከአቶ

ዕውቅና የሌው ችግር ከመፍትሄ ማን አስደርሶት?!

ምስል
እንዴት? መቼ? በምን ሁኔታ? ስለምንስ? ዕውቅና የሌለው ችግር  ከመፍትሄ ማን አስድርሶት? "ንጉሥ በፍርድ አገሩን ያጸናል፤ መማለጃ የሚወድድ ግን ያፈርሰዋል።"  መጸሐፈ ምሳሌ ፳፱ ቁጥር ፬ ·        መ ራራ መነሻ። https://www.youtube.com/watch?v=v1-4DqsofQw የራያ አማሮች በትግራይ ቅኝ ገዢ ወራሪዎች የሚደርስባቸው እንግልት ግድያና የማንንት ነጠቃ። https://www.youtube.com/watch?v=cUE6uDsTPW4 Ethiopia Special News የወልቃይ ስቃይ እየበረታ መቶዋል October/5/2018 https://www.youtube.com/watch?v=szp63jqOiXs ራያ አላማጣ ከትግራይ ጨፍጫፊ ሰራዊት ጋር ፍጥጫ 7 አማሮች ተገድለዋል ·        እ ምታን በዕድምታ፤ ኡኡታን ለሰርክ … አሁንም ጩኸት ሆነ። አሁንም እሪታ አለ። አሁንም ስጋት አለ። አሁንም መከራ አለ። ህፃናት ያለቅሳሉ፤ እናቶች ያነባሉ፤ አዛውንቶች ኡኡ ይላሉ። ማን አላቸው እና ያልቅሱ ... ፈጣሪ ከሰማቸው። አሁንም የታቀደ ጥቃት አለ። አሁንም ለቅሶ አለ። አሁንም መሰደድ አለ። አሁንም ተስፋ ማጣት አለ ለአማራ። አሁንም መኖር ተከልክሏል። አሁንም መተንፈስ አያቻልም - አማራ። አሁንም ችግሮች በአይነት ተደርድረዋል በተለይ ለአማራ። አሁንም አሳሩ ውጧታል አማራን። እንዴት ይፈታ? መቼስ ይፈታ? በምን ሁኔታስ ይፈታ? ስለምንስ ችግሩ አዬለ? መቼ ይፈታ ቢባል ችግሮችን ለመፍታት ለችግሩ ዕውቅና መስጠትን ይጠይቃል። የወልቃይት የራያ የጠገዴ የመተከል ችግር፤ አገራዊ ችግር ነው ተብሎ አይታወቅም። ተጋድሎውም እ

ልዕልት ርዕዮት አለሙን እስኪ እንዴት ባጀሽ ልበላት።

ምስል
ትናንትን ዛሬ በምልስት እስኪ ይቀፈው? ወርዱ ከቻለው?   „በሰዎችና፡ በመላእክት፡ ልሳን፡ ብናገር፡ ፍቅር፡ ግን፡ ከሌለኝ፡ እንደሚጮኽ፡ ናስ፡ ወይንም፡ እንደሚንሽዋሽ ው ፡ ጽናጽል፡ ሆኜአለሁ። ትንቢትም፡ ቢኖረኝ ፥ ምሥጢርን፡ ሁሉና፡ እውቀትን፡ ሁሉ፡ ባውቅ፡ ተራሮችንም፡ እስካፈልስ፡ ድረስ፡ እምነት፡ ሁሉ፡ ቢኖረኝ፡ ፍቅር፡ ግን፡ ከሌለኝ፡ ከንቱ፡ ነኝ። ድሆችንም፡ ልመግብ፡ ያለኝን፡ ሁሉ፡ ባካፍል፥ ሥጋዬንም፡ ለእሳት፡ መቃጠል፡ አሳልፌ፡ ብሰጥ፡ ፍቅር፡ ግን፡ ከሌለኝ፡ ምንም፡ አይጠቅመኝም።“ ( ዬሐዋርያው ዬቅዱስ ጳውሎስ መልዕክት ወደ ቆረንቶስ ሰዎች ምዕራፍ ፫ ቁጥር ከ፩ እስከ ፫ )  ከሥርጉተ© ሥላሴ 21.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ·        ማሰብ እና ማግኘት ጋዳ ናቸው። ልዕልት ርዕዮት አለሙን ዓይኔን በዓይኔ የማዬት ያህል ነበር የማስባት። እጅግም እሳሳላት ነበር የዛሬውን አያድርገው እና። ከእስር መፈታቷን ብቻ ሳይሆን የብርታትን እኩልነት ብርሃን ትሆናለች ብዬም በጽኑ አስባት ነበር። መመኘት ከልካይ ስሌለበት የውስጤ ሐሴት ትሆናለች የሚል ብሩህ ተስፋ ሰንቄ ነበር መፈታቷን የጠበቅኩት። የሚገርመው የእሷም የእህቷም መጠሪያ ሥም የእኔም  የእህቶቼም ነው። ሥምም ትርጉም ይሰጣል የውስጥ ሲሆን። እናም እጅግ አቅርቤ አያትም ነበር። በመጨረሻ ግን አሜሪካ ከገባች በኋ ዋላ ለእነዛ ካቴና ላይ ላሉ ነፍሶች ብጣቂ አዘኔታ ስታጣ ነፍሴን ጨነቃት፤ እጅግ ካዘንኩባቸው ጥቂት ነፍሶች አንዷ እሷው ሆነች። አሁን በቅርቡ በጀግኒት እማዋይሽ አለሙ ጉዳይ ታታሪ አቶ ተሎሳ ቃለ ምልልስ ያደረገላት እህት ስትናገር በስደተኛ እህቶቿ ላይ ፊርማ