ልጥፎች

ኑሯችን ኮንፓሳችን እና ካንፓሳችን ነው! መለመላ ያሰቀረ ሙግት - ተደመጠ በዋልታ።

ምስል
የህሊናን ቁመና መለመላ ያሰቀረ  ሙግት። „እግዚአብሄር፤ በጸሐይ ጮራ እንደ ደረቅ ትኩሳት፣ በአጨዳም ወራት እንደ ጠል ደመና ሆኜ በማደሪዬ  በጸጥታ ተቀምጬ እመለከታለሁ ብሎኛልና። ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ ፲፰ ቁጥር ከ፬ እስከ ፭“ ከሥርጉተ©ሥላሴ  29.11.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። በማለዳ የመጀሪያው ጉዳዮ ኢትዮጵያ እና አብዩ እስተ ሌጋሲው እንዴት እንዳደሩ ማረጋገጥ ነው። አንዳንድ ቀን ከንጋቱ 5 ወይን 6 ሰ ዓት ላይ ሁሉ አያሁኝ መረጃ። ምክንያቱም በዚህ በሸር በዘለበ የፖለቲካ ፍልስፍና ቀኑንም ሌሊቱንም አላምነውም። ስለዚህም ከአዬሁ፤ ካጣራሁ በ ኋዋላ የምስጋና ጠሎቴን አድርሼ ወደ ዕለቱ ውሉዬ ጉዞ አደርጋለሁኝ ማለት ነው። ዛሬ ደግሞ አንድ ሙግት አዳመጥኩኝ በቀደመው አጠራር የእኛ ልብ ውስጥ በነበረበት ወቅት  ከአብርሽ ጋራ። በ አሁን ደግሞ ከአቶ አብርሃም ደስታ ከ አረና ትግራይ ለሉአላዊነት ዴሞክራሲ ሊቀመንበር ጋር የዋልታ ቴቮዥን ሞጋች ጋዜጠኛ ጋር የነበረውን ውይይት ከውስጤ አዳመጥኩት። ዋው! ድንቅ ነበር። „አብርሽን“ ይህን በመሰለ የነጻነት አርበኝነት  እናውቀው የነበረው። https://www.youtube.com/watch?v=FmeGfeOaM_I&t=5s Ungerecht (injustice) neue አንድም ጹሑፍ ጽፌ ነበር የሁለት አገር ስደተኛ የሚል ዘሃበሻ ላይ ወጥቶልኝ ነበር፤ ይህ አጭር ፊልም ደግሞ ብዙ የሎቢ ተግባር የተከወነበት ነበር። ·        ወግና ቅኝት ተ ልዕልት ትዝብት ጋራ በቀለበት። አሁን ወደ ቀደመው ምልሰት ይሁን ከወንድማዊ ዕሳቤ ወደ የፖለቲካ ድርጅት መሪነት ሰለሆነ አንቱ አቶ እያልኩ ጥቂት ትዝብቴን ላጋራችሁ ወደድኩኝ - በጥዋቱ። ውዶቼ እኔ

ዕውነትን መወገን ትውልድን ያንጻል። ለእውነት ቀጠሮ አያስፍልጋትም!

ምስል
ቋንጣ። „ምን እንኳን በለስም ባታፈራ፤ በወይን ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፤ የወይራ ሥራ ቢጎድል፤ እርሾችም መብልን ባይሰጡ በጐችም  ከበረት ቢጠፉ፤ ላሞችም በጋጥ ውስጥ ባይገኙ እኔ ግን  በእግዚአብሄር ደስ ይለኛል፤ መዳድኃኒቴ አምላክ ሐሤት  አደርጋለሁ።“ ትንቢተ ዕንባቆም ምዕራፍ ፫ ከቁጥር ፲፯ እስከ ፲፰ ከሥርጉተ©ሥላሴ  28.11.2018 ከገዳማዊቷ ሲወዘርላንድ። ·       እ ፍታ። ሴት ልጅ ሁነኛ ክንድ ሳይኖራት ፖለቲካ ውስጥ ተሳትፎ መጀመር እኔ ባለኝ ተመክሮ እንደ እብደት ነው እማዬው። መከራ ብቻ ሳይሆን መኖርን የሚቃማ አሳር ነው። የማ ቆጨው በራስ ውሳኔ ስለሚሆን ብቻ ነው እንጂ ነገር ሴት የፈተና ተፈጥሮ ነው ያለው።  እንዴት አደራችሁ ዋላችሁ አመሻችሁ ውዶቼ አዱኛዎቼ። መቼም  ለኢትዮጵያ ሴቶች አዲስ ዘመን ቦግ ብሎ ብሩኽ ሆኖ ወጥቷል - ዛሬ ላይ። „ለእግዜር አይቀርበት ለሰው አይቀርበት ሰሌ ከሰራው ቤት እኛ ገባንበት“ ይላል የጎንደር ሰው ሲተርት። ገና ተወዳድራ ብታሸነፍ ተብሎ አንዲት ነፍስ ስንት ፍዳ ተከፈለ። ስንት መከራ ታዬ። ሥሟን የሚያነሳ የሚዋሳም አሳሩን ከፍሏል፤ ዕውቅናው ተቀባይነቷ እዬጎላ ሲመጣ ይህቺ ሽንብራ ከሰነበተች ዓይነት በሴራ ደቦ ከፖለቲካ ትግል የተገለለች ቅን ነፍስ እነሆ ዛሬ  የኢትዮጵያ አሉ የሚባሉትን የፓለቲካ ድርጅቶች ሊቀ ሊቃውንታትን ጉባኤ ከጠ/ሚሩ ጀምሮ የስብሰባው መሪ ሆና ጉብ አለች። ቅብዐ ያለው ነፍስ እንዲህ ነው። የፈለገው ነገር ቢገደብ፤ አጥር ቢሰራ፤ ክትር ቢበጅ ቅብዕ ካለ አይቀሬ ነው። ቅኖችም እንዲህ ሲገኙ መገናኛውን በቅኔ ዘጉባኤ ይቃኙታል እንዲህ ...  አሁን የዛሬ ዓመቱን ጉግስ ላሰበ ሰው ዛሬ የክብርት ዳኛ ብርቱካን ሜዴቅሳን

ተመክሮ ለመከረው ክብር ይገባዋል!

ምስል
ብስለት። ተመክሮ ለመከረው ክብር ይገባዋል! „ቀን የሚያመጣው ምን እንደ ሆነ አታውቅምና ነገ በሚሆነው አትመካ።“  መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ከሥርጉተ©ሥላሴ 27.11.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ሊሂቃኑ የኢትዮጵያን የምሥራች ቀን ተገኝች ክብርት ትናፍቅሽ ሲባል አስከዛው ድረስ ነው እያሉ በሚመጻድቁበት ማግስት ትናንት አቶ ሌንጮ ለታ አንድ ቁም ነገር ላይ እርገት አድርገዋል።  ከዚህ ቀደመም የሸግግር መንግሥት አያስፈልግም ብለው ፊት ለፊት ወጥተው የሞገቱ ነበሩ፤ የዶር መራራ ጉዲና ህሊና የተጽዕኖ ፈጣሪዎችን የአንድነት መንግሥትን አዲስ ሽል ይዞ ብቅ ሲል፤ ሌላውም የሽግግር መንግሥት አሁኑኑ በማለት መለከቱን ሲነፋ አሳቸው ግን ግን አያስፈልግም ብለው ነበር አቋም የያዙት። ወደ አገር ሲገቡም  አጀብም፤ ጭብጨባም፤ ስልፍም አላስፈለጋቸውም እዩን እዩን  አላሉም እንደ ማለት። በዛው ሰሞናት ደግሞ ከአህዱ ራዲዮ ጋር ውይይት ሲያደርጉ ስለምን ያን ያህል ወጣት በባዶ እጁ ሲረግፍ ያልነበረ ድረጅት አሁን ያዙኝ ልቀቁኝ ማለቱ ግርም ብሏቸው የት ነበር የዳውድ ኢብሳ ሠራዊት  ያን ጊዜ ወጣቶቹ ሲያልቁ በጥይት ሲቆሉ ሲሉ ተደምጠዋል።  በአህዱ ራዲዮ ቃለ ምልልስም ምርጫው በተያዘለት ገደብ ይከውን ብለው ግን መከወኑ አሁን ያለው ለውጥ ህጋዊ እውቅናውን ለማስገኝት ቢሆን የሚል ዕድምታ ነበረው እሳቤያቸው በቅጡ ከተፈተሸ። ትናንት ደግሞ ልብ ያለው ነገር ገልጸዋል፤ ራሳችን በ እርጋታ እሰክናደራጅ ድረስ እኛ በመጪው ምርጫ አንሳተፍም ለውጡ መሠረት እንዲይዝ እንተጋለን ብለዋል። ደፋር እርምጃ ነው ።  ደፋር እርምጃ ነው እምለው በምርጫው አለመሳተፋቸውን አይደለም። ምርጫ ለመሳተፍ የተመዘገቡት ፈሪዎች ናቸው