ልጥፎች

ብአዴን ከአቶ ሌንጮ ለታ የተቀባይነት ጠብታ ይለምን።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  የ80ሺህ ህዝብ ሰቆቃን ማነው አማጩ?  „እኔም ባሪያህ ከትንሽነቴ ጀምሬ እግዛብሄርን እፈራ ነበር“ መጽሐፈ ነገሥት ቀዳማዊ ፲፰ ቁጥር ፲፪ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie  19.02.2019 ከእመ ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። የሚቀድመውን ማወቅ እንዴት ያለ ብልህነት መሰላችሁ ውዶቼ? ግን እንደምን አላችሁልኝ። እኔ እህታችሁ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ። እኔ የሰኔ16ቱም ግብታዊ የድጋፍ እና የምስጋና ሰልፍ፤ የወርሃ ሀምሌ የሰሜን አሜሪካ የጠ/ሚር ጉዞም፤ መጨረሻ ላይ የብአዴን ጉዞን አክሎ ምቾት ያልሰጠኝ ዕጣ ነፍስ ነበርኩኝ። በሰኔ 16ቱ በቅጡ የተደራጀ አለመሆኑ ብቻ ሳይሆን አቅሙ ከታዬ ጠላት እንደ አሸን እንደሚያፈራበት የታለመ ነበር።  አደጋውንም አሳምሬ ገልጫለሁኝ ወዮለሽ አዲስ አባባ ብዬም ። ስልፉ የአዲስ አባባ የመከራ አምራች ስለመሆኑ አስረግጬ ገልጫለሁኝ። አማካሪም፤ አዳምጫም አልነበረም ያው የገበረ ተገብሮ ቀረ። እንደ ሰማዕቷ ሽብሬ ደሰለኝ ወላጆች ሁሉ አካሉን ያጣም አካሉን አጥቶ ቀረ።  የመሸበትም መሽቶበት ቀረ። የዳመነበት ዳምኖበትም ቀረ። ·        ዝበት እና እርቀት። የሀምሌው የጠ/ሚር እና የሚያርቧቸው ነፍሶች የስሜን አሜሪካ ጉዞ በሚመለከት ከዛ በፊት የስሜን አሜሪካ እስፖርት ፌስቲባል ለመገኘት ጠ/ሚር አብይ አህመድ ባሳዩት መልካም ፈቃድ ላይ የነበረው ሳንክ፤ የነበረው የጦፈ ውግዘት የነበራችሁበት ነው።  እኔም ያን ጊዜ የሚጠቅማቸው እንደሆን ይሳካ፤ የማይጠቅማቸው ከሆነ ግን በጥበቡ አማኑኤል የፈቀደውን ይፈጽመው፤ ግን ተቀናቃኞቻቸው የቅናት አማርኛ ነው የሚያራምዱት ሁሉ ብዬ ጽፌ ነበር።   እንደዛ በ90

የምዕት ፈርጧን አርቲስት ኢፋ /ኢቢታ/ ፔሩን "በተባረከች አገር ለተባረከ ትወልድ" ተስፋ ውስጥ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ለውጡ እንደ ዝናሽ ንዑድ መንፈስ የእኩልነት ማህደር ቢሆንልን። „እግዚአብሄር ለሰው ልጆች ይደክሙበት  ዘንድ የሰጣቸውን ጥረት አይቻለሁ።“ መጽሐፈ መክብብ ፫ ቁጥር ፲ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 18.02.2019 ከእመ ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። ጥሞና መልካምነቱ ብዙ ነገርን ከውስጥ ለማዬት ይረዳል። ሳተናው ድህረ ገጽ ስገባ የማነባቸው፤ ዩቱብ ስከፍት የማደምጣቸው ነገሮች መከፋቴን አሳየሉበት። ስለምን ብትሉኝ በ2008 ላይ የነበረው ድቅድቅ ጨለማ እና „ሰከን በል“ የአርቲስት ይሁኔ በላይ የህሊና ተቋም እኔን ያልተለመዱ እርምጃዎች ያስወሰዱኝ የጭንቅ ወቅት ነበሩና። እነዛ ያልተለመዱ እርምጃዎቼ ጥቋቁር ሰለነበሩ ያን መልክ ለማሳያዝ ደግሞ የግድ ጠ/ሚር አብይ አህመድ ወደ እጩ ጠ/ሚር ሲመጡ ማቃናት ነበረብኝ። እናም በድፍረት ያን ቁስለቴን የሚሸር ቀን ፊት ለፊት ዋዜማ ላይ ነው ብዬ የቀደመውን የጭንቀት መንፈስ የሚረገብ ጹሑፍ ጻፍኩኝ እና ለኩኝ። ኢህአዴግ ውስጥ የነበረው የለወጥ አዬር በጤናዳምነት በቅንነት ነው የተመለከትኩትና። ያተስፋዬ በ ኢህዴግ ውስጥ ከተሳካ ያን የመሰለ ምሬት ከእንግዲህ ለመላክ አላማሰቤን ስስበው እራሱ ጤናዬን መለሰለኝ። የዛሬውም የቀድሞዎችም ኢህአዴግ ላይ የነበረው ጠባሳ መሻሪያው የተስፋ ዘመን መጣ በሚል በትልቁ ሰፋ አድርጌ መንፈሴን እርጋ አልኩት። በዛ የውስጥ ቁስለት ውስጥ የታደሙ መንፈሶች እንደ እኔው ተስፋ ያደርጉ ዘንድ ደግሜ መማጸን ስለነበረብኝ ነው የማቃኛ ሌላ ደብዳቤ የጻፍኩት ለሚያደምጡኝ። አሁን የምሰማው የማዬው የማዳምጠው ደግሞ ለዬት እያለብኝ ነው። ዛሬ ጥዋት ከቀደመት አንጋፋ ጋዜጠኞች ውስጥ አቶ ኆኀተብ

አይዋ ምንትሶ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  አይዋ ምንትሶ። „በክፉዎች ምክር ያልሄደ በሃጢያተኞች መንገድ ያልቆመ እሱ የተመሰገነ ነው። በእግዚአብሄር ህግ ደስ ይለዋል።“ መዝሙረ ዳዊት ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie  18.02.2019                                     ይህ ለከብት ህልውና ብቻ ነው። እንዴት ናችሁ ውዶቼ? ደህና ናችሁ ወይ? ከዚህም ከዚያም፤ ከዚያም ከዚህም፤ እንዲህ ወደ ማዶ፤ እንዲያ ወደዛም ወደ ፈረፈሩ ... ቅይጥ ቅብጥር ምንት ሶ ነት ይደመጣል። ምኑ ተጨውቶ? በዚህም በዛም ቢመጣ። በዚህም በዛም ቢባዛም ጽናት በሌለው ዓላማ ዘመን ሰጥ ገጠመኞችን ዳክሮ ማዳከር አይዋ ምንትሶ ዛሬም እንደትናቱ እያስተናገደ ነው። በየሉም የሌሉዮሽ አዲስ ጠናና ቅብጥርሶ፤ ብልዝ ብርዳብርድ ባለው ሞ ግ ድ ባልተሰራለት ትናጋ ቢሉት ያም መብት ነው። ይቻላል እንደማለት። መብት ሲሆን ታዲያ በዬለም በተከዘነው አምክንዮ ውስጥ እንደ ቀደመው በማባጨል መሆን አይገባውም ነው ቁምነገር። ቅድሚያ አንድ ሁሉት ነገር ይዞ ብቅ ከማለት እራስ በዛ አመክንዮ ውስጥ ስለመኖሩ ፈተሽ ማድረጉ የተገባ ነው። ታዛቢዎች ስላለን። ያው የምንትሶ ነገር ሲረታ ደግሞ በምናምንቴው እሰኪጋፍን ድረስ … አይዋ ምንትሶ አዚማም ነው። መቀመም ያውቅበታል። ቀምሞ ድብን ያደርጋል። የዋዛ ለሴራ ማን ብሎት ተፈጥሮበት የለም።     ለነገሩ አድጦ አድጦ አንደላልጦ አንደላልጦ አሁን መለመላ ሲቀር ያው በፈረደበት ፍርደኛ ወደ አይዋ የኔታ የዋህዮት ተዝካሬን አውጣልኝ በሏል። ሲፍከረክ እንደለመደበት ማጣፊያው ሲያጥረው ጥግ ሁነኝ የሙጥኝ መባል የተለመደ ነው።  አይዋ ምንትሶ ትናንትም ምንትሶ ዛሬም ምንትሶ ነገም ምንትሶ