ልጥፎች

ሰባት ለአንድ ከተረቦች ሁሉ የላቀው የጠ.ሚር ቢሮ ድራማ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ሰባት ለአንድ ከተረቦች ሁሉ የላቀው የጠ.ሚር ቢሮ   ድራማ።  „በፊቱ ካለው ብርሃን የተነሳ ደመናትና በረዶ የእሳት ፍምም አለፉ።“ መዝሙር ፲፯ ቁጥር ፲፪ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 08.03.2019 ከእመ ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። ጅብ ወለደ። አዎን ኢትዮጵያ በጸሐይ ውስጥ ዝናብ ሲኖር እንደዛ ነው የሚባለው። ዛሬ ሙሉ ቀን ወጀብ ነበር። ማምሻ ላይ ደግሞ ጸሐይ ወጥቶ ነበር። እንደገናም ይዘንባል። እናም ጅብም ቪንቲ ላይ ወለደ ማለት ነው። ትናንት ማምሻ ላይ አንድ ቧልት አዳምጬ ነበር። ዛሬ ጥዋት ሳተናው ላይ ስገባም አነበብኩት። በቀደመው የደርግ ጊዜ ዘመቻ ዘመቻ የሚባል ነገር ይዋቀር ነበር። አሁን ደግሞ ኮሜቴ፤ ኮሜሽን ሆኗል። ሌላ ሥራም አጣ የጠ/ሚር ጽ/ቤት ... አደናግሬ! የማንነት የወሰን ኮሚሽን የሚባል በዓዋጅ ተደራጅቷል። በፓርላማ ሹመቱ ከጸደቀ በሆዋላ ደግሞ የፈለጋችሁን ማስገባት ትችላለችሁም ተብሏል። ይህ በራሱ ሳይመረመር እንደተሸፈነ የታለፈ ገማና ነው። እኔ ጥሞና ላይ በነበርኩበት ጊዜ ስለነበር ብዙም አልሄድኩበትም ... ብቻ ዋዛ አና ብሏል ... ሜጫም እንዲሁ ... የሜጫው ሱናሜ እማ ምን ኡጡ ...  ግብታዊ ነገሮች በቃ እንደወረደ ሆነ  ይህም ብቻ አይደለም ተፎካካሪ/ ተቃዋሚ/ ተቀናቃኝ የሚበሉትም እጃቸውን ለኦዴፓ ሰጥተው በዚህ ተግባር ኮሚሽን ላይ ተሰማርተዋል። ቧልቱ እንዲህ ነው የተጀመረው። ተዋህደዋል ማለት ነው በትርጉም ሲቃና። አሁን ደግሞ ይህ አካል እያለ ለአዲስ አባባ እና  ለኦሮምያ ሌላ ኮሜቴ አደራጅቻለሁ ብሎ ይተርባል የጠ/ሚር አብይ አህመድ ቢሮ። በነገራችን ላይ ዛሬ የፕሬስ ጉባኤ ነበር አሉ እንዲህ ወደ አ

ትዕግሥት ሲያልቅ ፍቅር ይሰደዳል። የሜንጫ ሱናሜ ...

 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ትዕግሥት ሲያልቅ ፍቅር ይሰደዳል። „በፊቱ ካለው ብርሃን የተነሳ ደመናትና በረዶ የእሳት ፍምም አለፉ።“ መዝሙር ፲፯ ቁጥር ፲፪ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 08.03.2019 ከእመ ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። ·        መንገድ። ጤና ይስጥልኝ ውዶቼ። ደህና ናችሁ ወይ። ዛሬ ወጀብ መሳይ አለ እንዲህ ወደ ቪንቲ። መስኮቴንም እዬነቀነቀው ነው። ኢትዮጵያም የከፋ ወጀብ አለ። የአብይን ካቤኔ ሊንጥ የተሰናዳ። ገና አልፈነዳም ግን የታመቀ መከራ ፊት ለፊት ተደቅኗል። ያው ሽግግር እያደረግን ነው ትዕግሥት አልቆ ፍቅርን ለማሰደድ ። ሻንጣዎቹ ፓክን ፓክን ሆነዋል። የሰው ልጅ ፍቅር ለመስጠት ቅን መሆን አለበት። ተጠራጣሪ ሰው ፍቅር መስጠት አይችልም። እንዲህ ዓይነት ፍጥረት በህይወት ዘመኑ ሁሉ ፍቅርን ሳይሰጥም፤ ፍቅርም ሳይቀበል ዘመኑ ይጠናቀቃል፤ ለነገሩ መስጠትም መቀበልም ፍቅር ከሚያውቅ ቅን ነፍስ የሚገኙ የፈጣሪ ስጦታዎች ናቸው። ብዙ ጊዜ ለማናቸውም ነገር ስጦታ የሚያዘጋጁ ሰዎች የፍቅር ቅን ሰዎች ናቸው። ለእኔ ፍቅርን የሚፈጥረው ቅንነት ነው ብዬ አስባለሁኝ። ፍቅር ለመስጠት ንፎጎች ምክንያታቸው ነገ እንዲህ ቢሆን፤ ነጋ እንዲያ ቢሆን በማለት ወቀሳን የሚሸሹ ብቻ ሳይሆን ተፈጥሯቸው በአሉታዊ ብክል ፍልስፍና የሚገዛ ይመስለኛል። የሆነ ሆኖ እኔ የኢትዮጵያ ህዝብን ስመለከተው ፍቅር ለመስጠት ለጋስ ነው። ፍቅር ለመቀበልም ለጋስ ነው። የኢትዮጵያ ህዝብ ፍቅር ሲሰጥ በትህትና አክብሮ ነው። ፍቅር ሲቀበልም በትህትና በአክብሮት ነው። ሲጓደል ደግሞ አብዝቶ ይታገሳል። የኢትዮጵያ ህዝብ እንደ ህዝብ ቁንጥንጥ አይደለም። የኢትዮጵያ ህዝብ የሰከነ ነው። የሚገር

የዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን ብሄራዊ ጥሪ እና ዕድምታው ተነሆድዕቃው።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  የዓለም አቀፍ የሴቶች  ቀን ብሄራዊ ጥሪ እና ዕ ድ ም ታ ው  ተነሆድዕቃው። „እግሮች እንዳይናወጡ አረማመዴን በመንገድህ አጽና“  መዝሙር ፲፭ ቁጥር ፭ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 09.03.2019 ከእመ ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። ·               ክብር ሆይ!  ቅንነተዎትን እባከዎት ለኦነጋውያን ምርኮኛ አያድርጉብን! መክፈቻ። ጤና ይስጥልኝ ውዶቼ እንዴት ናችሁ? ደህና ናችሁ ወይ? የኢትዮጵያ ፖለቲካ የሴራ ፖለቲካ በመሆኑ ከዚህ የሴራ ፖለቲካ የምንሻገርበት ቀዳዳን ለመጠቀም ብልህነት እና ማስተዋል እንጂ ግትርነት ሆነ ጥርጣሬ አግባብ ስላልነበረ የኦህዴድን / ኦሮማራን / ጉዞ አቅርበን የእኛ አድርገን የማዬታችን ጉዳይ የተገባ ነበር። ይህም በመሆኑ ዛሬ ያለው መተንፈሻ ቧንቧ ተገኝቷል።   ልብን የገለጡ ቅንነቶች ሁልጊዜም በፈጣሪያቸው ዘንድ የተከበሩ ናቸው። እኔ እንደ ተዋህዶ ልጅነቴ የትኛውም አካል ዓላማ አለኝ ብሎ ሲነሳ በቅንነት ልቤን ንጹህ አድርጌ ነው የምቀበለው። ወይንም የማይመቸኝ ከሆነ ዝም ነው የምለው። አልደግፍም አልቃወምም። ለምሳሌ በግንቦት 7 ምስረታ ይሁን፤ በግንቦት 7 የኤርትራ ጉዞ ቅኑን ልቤ ለግሻለሁኝ። ለዛውም ያን ያህል ወጀብ በነበረበት ወቅት እነሱም አይዞሽ ሳይሉኝ።  ድርጅቱ በተመረዘመበት የስሜን ኢትዮጵያ ጠል ፖለቲካ አማካኝነት። እኔ ግን በምችለው ሁሉ ጉዲት እስክባል ድረስ ከዚህም ያለፉ የግል የሰላም ህወከቶችን አክሎ አሰተናግጃለሁኝ። ያን በማድረጌ ግንቦት 7 ፈተናው ሳያልፍ ሲቀር አይጸጽተኝም። ቅንነት የሚጎዳው ተቀላቢውን እንጂ ቀላቢውን አይደለም። ስለምን እዮር አለና። የሆነ ሆኖ