ልጥፎች

የአቶ ነአምን ዘለቀ ከግንቦት 7 ራስን ማግለል ዕድምታ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  የራስነገር። „አንተ ፈጣሪያችን ግን ቸር ነህ ይቅር ባይ ነህ፤ የምትታገሥ ነህ፤ ከሀሊነትህን እያወቅን ብንበድልም ባንበድልም፤ ያንተ ወገኖች   ነንና በቸርነትህ ሁሉን ትሠራለህ። ነገር ግን ያንተ ወገኖች   እንደ ሆንን እናውቃለን።“ መጽሐፈ ጥበብ ፲፭ ቁጥር ከ፩ እስከ ፪ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 20.03.2019 ከእመ ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። ·        ከውስጥ ስለማዬት። የእኛ ነገር እንዲህ ነው ተሰበሰበ ሲባል መበተን፤ ተበተነ ሲባል መሰብሰብ። ተቃና ሲባል መጉበጥ፤ ጎበጠ ሲባል ደግሞ መቃናት፤ ፈሰስ ሲባል መ ለ ቀም፤ ተለቀመ ሲባል መፍሰስ እኛ እንዲህ ነን። በቀለ ሲባል መድረቅ፤ ደረቀ ሲባል ማጨብጨብ፤ ሞላ ሲባል መጉደል ጎደለ ሲባል መሙላት፤ ሞላ ሲባል መፍሰስ፤ ፈሰሰ ሲባል ክው ብሎ መድረቅ ዕጣ ፈንታችን ይኸው ነው። ሰሞኑን አንድ ዜና አዳመጥኩኝ። ሳዳምጠውም ደነገጥኩኝ። ጋደም ብዬ ስለነበር ቀና አልኩኝ እና በማስተዋል ዜናውንም ሀተታውን አዳመጥኩኝ አቅራቢው ጋዜጠኛ ሄኖክ አለማዬሁ ነበር። የሰማሁት ከዘሃበሻ ኦፊሻል ድህረ ገጽ ላይ ነበር። በምልሰት ደግሜ አዳመጥኩት። ድንጋጤዬ አብሮኝ ቆዬ። በዚህ ወቅት ይህ ይሆናል ብዬ አልገመትኩም ነበር። የእውነት። አቶ ነዓምን ዘለቀ ከግንቦት 7 ራሳቸውን ማግለላቸው ነበር ዜናው። ዜናው ከዘሃበሻ ስለገኘሁት አልተጠራጠርኩትም። ግን በጹሑፍ የሰፈረ አግኝቼ እስክመረምረው ተግ አልኩኝ። ትናንት ሚዲያዎች ላይ ጎልቶ የወጣ የውይይት አጀንዳ ይሆናል ብዬ አስቤ ነበር። አብሶ በደከሙለት ሚዲያ በኢሳት ከዜና በስተቀር እንደ አቶ ዛዲግ አብርሐ ያህል እንኳን ቁብ አልተሰጠውም ወይንም ክብር አልተሰጠውም

ኢትዮጵያስ እራሷስ እዬተፈናቀለች አይደል

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ኢትዮጵያስ እራሷስ እዬተፈናቀለች አይደል። "ይገባቸዋልና ስለዚህ ነገር ጣዖቶቻቸውን በሚመስሉ አጋንንት ጠፉ፤  በብዙ የሚሆኑ ትንኞች ክፉ የሚሆኑ እንዚህ ተጨነቁ።"  መጽሐፈ ጥበብ ምዕራፍ ፲፮ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 20.03.2019 ከእመ ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። እንዴት ናችሁ ውዶቼ? ደህና ናችሁ ወይ? እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ? አላዛሯ ኢትዮጵያ ታማለች። በሁለመናዋ እዬተጎሳቆለች ነው። እሷ እራሷ እተፈናቀለች ነው። በመንፈስ፤ በሥነ - ልቡና በሁለመናዋ ነቀላ እዬተካሄደባት ነው። የዚህ ምንጩ ማነው? መሠረቱስ ምንድን ነው? ·        ጋኔል። ለዚህ ሁሉ ምንጩ እና መሰረቱ የሄሮድስ መለስ ዜናዊ ጋኔል ማንፌስቶ ነው። የ አቶ ሌንጮ ለታ እና የሄሮድ መለስ ዜናዊ መግለጫም ነው ህገ መንግሥት የተባለው። ሲቀመም በሻብያ ውሃ ልክ ነው። ይህ ማንፌስቶ በኖረበት አራት አስር ዓመታት ሁሉ በእያንዳንዱ ሰከንድ ማለት ይቻላል፤ ጣሊያን ወረስ የሆነውን ኢትዮጵያን ጨርሶ የማፍለስ ፍልስፍ ዶክተሪን ነው የተከተለው።   ለጋኔሉ ሰነድ እውን ለማድረግ አጥፊ አረም ሲተክል ነው የኖረው የሄሮድስወሌንጮ የሚባትት ክፉ መንፈስ።  አሁን ነው እኔ እዬታዬኝ ያለው ያ ሙት መንፈስ አሁንም እያመሰ ስለመሆኑ። ያ ሰይጣናዊ መንፈስ አሁንም የዘራውን እያጨደ ሳይሆን እኛኑ ቀጥቅጦ ገዝቶ ደግሞ አሁንም አስደግድጎ እያሳጨደን ይገኛል። የሁለቱ የሙት መንፈስ አንዱ በአካል ሌላው በደመንፈስ እንሆ ኢትዮጵያን እያፈናቀላት ነው ከባዕቷ። ኢትዮጵያዊነት ማለትም መሆንም በአደባባይ በአዋጅ እዬተራደ እዬተቃጠለ እዬወደመ ነው የ

አዲስ አበባዬ የልዕልት ሉሲዬ ዬድንቅነሽም ናት!

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  አዲስ አበባዬ የልዕልት  ሉሲዬ ዬድንቅነሽም ናት! „አንተን ማወቅ ፍጹም ክብር ናትና፤ አንተንም ማወቅ የነፍስ ክብር ናትና።“ መጽሐፈ ጥበብ ምዕራፍ ፲፭ ቁጥር ፫ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 19.03.2019 ከእመ ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። ጠላትም ወዳጅም እንዲያውቀው አይለያዩም! ቅኖቹ ታዳሚዎቼ እንዴት ቆያችሁልኝ? ሰሞኑን የሉሲ ጉዞ የሚል አንድ ቡድን በመላ ኢትዮጵያ ይንቀሳቀሳል። የተፎካካሪ የፖለቲካ ድርጅቶች በማይገኙበት ሁሉ ይለፍ ተስጥቶት ተልዕኮው ከተሳካ እዬሞከረ ነው … ለህሊና አጠባ ፕሮፖጋንዳ ሳይሆን መሬት የያዝ ተቋም ያስፈልገዋል። በዓዋጅ የሰው ህሊና አይታጠብም። በመሆን ውስጥ በተገኜ ቃል እና ተግባር ብቻ ነው ህሊና ሊጸዳ የሚችለው። የስሞታ ፖለቲካ በበቀል በሚጋገርበት በዚህ ወቅት አፍሶ መልቀም፤ ለቅሞ ማፍሰስ ከመሆን የዘለለ ነገር አይኖርም። በሳቢያ ላይ አትኩሮት ዘላቂ መፍትሄ አያስገኝም፤ በምክንያታዊ ችግሮች ከራስ የጀመረ ለውጥ ነው የውስጥ ሰላም ማምጣት የሚቻለው። መጀመሪያ የየትኛወም ሰላም የጉዞው አባልተኛው እራሱ በሰላሙ ውስጥ ስለመሆኑ ራሱን ያቻለ ሞጋች አመክንዮ ነው።  ኢትዮጵያዊነት ሳይቀበሉ በዕምነት ደረጃ፤ የኢትዮጵያን ሰላም ማስከበር አይቻልም። ልክ እንደ በዓዋጅ እንደተቋቋመው የእርቅና ኮሚሽን እና ማበርተኞቹ አይነት ማለት ነው። እነሱ እራሳቸው ከራሳቸው እና ከተልዕኮው እንብርት ከ ኢትዮጵያዊነት ጋር ምን ያህል እንደታረቁ ልብ እና ኩላሊት የሚመረምረው ፈጣሪ ያውቀዋል። ኢትዮጵያ በጎርፍ ፖለቲካ ስታታመስ ባጅታ አሁንም አዋጁም፤ ኮሚቴውም፤ ቡድኑም የሚመሰረተው በዛው በሸፈተ ልብ መንፈስ ነው። በዛ ላይ