ልጥፎች

የኦነግን ዓላማ ለመሸከም አቅም የለንም። አቅም ለማዋጣትም አንፈቅድም!

ምስል
 እንኳን ደህና መጣችሁልኝ  ምርመራ። ክፍል አንድ። „እግዚአብሄር ፍርድን በማድረግ የታወቀ ነው።“ መዝሙር ፱ ቁጥር፲፮ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 02.04.2019 ከእመ ዝምታ ሲዊዘርላንድ።                                                                                 ይህ የኦሮማማ አይዲኦሎጂ ትርፍ ነው ።  ውዶቼ ክብረቶቼ እንዴት ናችሁ ደህና ናችሁ ወይ? የበታችነት ባይረስ ፋሽታዊ ዕሳቤን እንደሚወልድ አሁን እያስተዋልኩኝ ነው። ፋሽታዊነት መንፈሱን የሚመራው መርህ ጥላቻ ነው። ጥላቻ ደግሞ የመንፈስ ሪህ ነው። ሥነ - ልቦናንም ያደቃል። ጠቡ ከሰውኛ ተፈጥሮ እና ስኬት ጋር ስለሆነ።    ይህ የመንፈስ ሪህ ለመፈወስ ደግሞ አላዛሯ ኢትዮጵያ መንገዱን ገና አልጀመረችውም። እርግጥ ነው ቀደም ባለው ዶር አብይ አህመድ የፈላስማው ዶር ኢትዮጵያዊ ፈላስፋ ከዶር ምህረት ደበበ ጋር ማይንድ ሴት ላይ አብረው ይሰሩ ነበር። እኔም የዶር አብይን መንፈስ የተዋወቅኩት በዚህ መስመር የፍቅራዊነት እንቡጢጣ ፕሮጀክቴን ስሰራ አፍሪካ ላይ ምን በመከናወን ላይ እንዳለ ሳስ ነው ያገኘኋቸው። ዶር አብይ አህመድ በፖለቲካው መድረክ ጎላ ብለው ከመውጣታቸው በፊት ሲወገዙ ፊት ለፊት ወጥቼ ለመሞገት ያስቻለኝም ያ የቆዬ ጥሪት ስለነበረኝ ነው። ሰውኛ ጠረን ነበራቸው። ተፈጥሮኛ ጠረን ነበራቸው። የ አገር ፍጹም ተቆርቋሪነት እሸት ጠረን ነበራቸው። ስለዚህም ነበር ደፍሬ እመመሰክረው የነበረው። ስለምን የህሊና ዕጠባ የሚጀምረው እውነትን በተፈጥሮው ልክ መቀበል ስለሆነ። ጠ/ሚር አብይ አህመድ ከእውነት ጋር ይዘልቃሉ ብዬ አስብም ነበር፤ እኔ ተስፈኛ ነኝና። ከ

የርዕሰ መዲናን ደህንነት ከአቅሙ በላይ ከሆነ የፌድራሉ መንግሥት ጠቅልሎ ገዳም ይግባ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡ።  የርዕሰ መዲናን ደህንነት ከአቅሙ በላይ ከሆነ   የፌድራሉ መንግሥት   ጠቅልሎ ገዳም ይግባ። „ በዚያ ዘመን ንጉሡ ሄርድስ መከራ ያጸናባቸው ዘንድ ከቤተ ክርስትያኑ በአንዳንዶቹ ላይ እጁን ጫነባቸው። “ የሐዋርያት ሥራ ምዕራፍ ፲፪ ቊጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie  01.04.2019  ከእመ ዝምታ ሲዊዘርላንድ። እጅግ የሚገርሙ እርስ በእርሳቸውም በጥፊ የሚጯጯሉ ጉዳዮች ይሰተዋላሉ በጠ/ሚር አብይ አህመድ ቢሮ። ግንባራችንም መንግሥታችንም የምንመራበትም አይዲኦሎጂ አለ፤ አቅም አለን ያሉት ጠ/ሚር አብይ አህመድ በሰሞናቱ ጋዜጣዊ መግለጫቸው የጋዜጠኛ እስክንድርን ጋዜጣዊ መግለጫ ግን አስግድበውታል። አሳግደውታል፤ ጉልበታቸውንም አሳይተዋል። በጣምም ፈርተውታል።  መንፈሳቸውንም እረፍት ነስቶታል። መሰከረም ላይ ማህል አዲስ አባባ በበቀል 5 ሰማዕትታ ደማቸው ሲዛራ በግፍ ይህን ያህል አልተጨነቁበትም ነበር። የቆሞስ ስመኘው በቀለ ህልፈትም ከመጤፍ አልቆጠሩትም። በወጣቶች እስር እና ድብደባም ህልፈትም ወጥተውም ያሉት አልነበረም። የሚገርመው ባለማስቲካው የጃዋር መንፈስ ሴክሬታሪ አቶ ንጉሡ ጥላሁን የሰጡት መልስ ደግሞ ግርም የሚያደረግ ነው። ለካናስ ጠ/ሚር አብይ አህመድ ሞጋች ሃሳብ ሲመጣ፤ አቅም ያለው ወገን ሲመጣ ይህን ያህል ይርዳሉ ማለት ነው። ምነው ፈሩት ይህን መንፈስ? ስንት አሉ የሚባሉ የፖለቲካ ሊሂቃን ጋር ቁጭ ብለው እዬተወያዩ አይደለም ወይ? ነው እነሱን አንደባልያቸዋለሁ በስብከት ብለው አስበው ይሆን? መቼም የህዝብ ማዕባል ከመጣ እጅግ የከፋ ነው የሚሆነው። ሰላማዊ ተጋድሎ በሁሉም መስክ የሚያደርግ ዝምታ ከመጣ

ግፋፎ ሲፈታተሽ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ  ግ ፋ ፎ  ሲፈ ታ ተ ሽ ። „ጠላቴ እንደ በደለኛ በእኔ ላይም  የሚነሣ ኃጢያተኛ ይሁን“ መጽሐፈ እዮብ ፳፮ ቁጥር ፯ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selasssie 01.04.2019 ከእመ ዝምታ ከሲዊዘርላንድ። ውዶቼ እንዴት አላችሁልኝ? እኔ እህታችሁ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ። አሁን ያው ከዋናው እልፍኜ ከቤቴ ከሳታናው ድህረ ገጽ ጎራ ብዬ ነበር። ግርም ብሎኝ ጡሁፎችን አነበብኩኝ። ይልቅ ልጅ አቶ ተክለሚኬኤል አበበ አንድ ሸጋ ሃሳብ እንስቶ አነበብኩኝ። አሁን እኔና እሱ ስንሟጋት ነው የኖርነው። እንደ እሱ የአጣጣፍ ዘዬ የሚመቸኝ ቢኖር የልዕልት ጽዮን ግርማ ብዕር ነበረች። ያው ሙግታችንም ከአቶ ወንድም ከልጅ ተክሌ ጋር ጤናም የሆነ ነበር። የሚገርመው ዛሬ ባዬሁት ጡሁፍ አንድ መሰመር ላይ ተገናኘኝ። እኔም እንደ እሱ ያለ ሃሳብ ነው ያለኝ። ስለተደረገው መልካም ነገር አመስግነን ምዕራፍ ሁለት ግን በነገር ዥዋዥዊት ሳይሆን መልክ ያለው ነገር መስራት ያለብን ይመስለኛል። https://www.satenaw.com/amharic/archives/65830 የአዲስ አበባ ባለአደራ ምክርቤት፤ ወደኢትዮጵያ ባለአደራ ምክርቤት ይደግ ( ልጅ ተክሌ ለዚህ ደግሞ እዮርም የሰማይ ምልክት ሰጥቶናል በዚሕው ቀን። መጋቢት አንድ ቀን ሁለት ሺህ አስራንድ። ዕለተ ሰንበት። ቤተመንግሥት የእስክንድርን ንቅናቄ አቅም ለመፈታተን ሲያሰላ እዮር ሉላዊውን ዓለም ያካተተ የሰማዕታት ምልክት ሰጠ።  የተሰባሰበው የጃዋርውያኑን መንፈስ ለማደንዘዝ ነበር። የሚዲያ ባለሙያ እና የፖለቲካ ሊሂቃን ያን እንጋታለን ብለው ታድመው ነበር … ቅዱሳን ደግሞ በባልደራስ አዳራሽ… ስለዚ