ግፋፎ ሲፈታተሽ።

እንኳን ደህና መጡልኝ
ፎ 
ሲፈ
„ጠላቴ እንደ በደለኛ በእኔ ላይም
 የሚነሣ ኃጢያተኛ ይሁን“
መጽሐፈ እዮብ ፳፮ ቁጥር ፯

ከሥርጉተ©ሥላሴ
Sergute©Selasssie
01.04.2019
ከእመ ዝምታ ከሲዊዘርላንድ።


ውዶቼ እንዴት አላችሁልኝ? እኔ እህታችሁ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ደህና ነኝ። አሁን ያው ከዋናው እልፍኜ ከቤቴ ከሳታናው ድህረ ገጽ ጎራ ብዬ ነበር። ግርም ብሎኝ ጡሁፎችን አነበብኩኝ።

ይልቅ ልጅ አቶ ተክለሚኬኤል አበበ አንድ ሸጋ ሃሳብ እንስቶ አነበብኩኝ። አሁን እኔና እሱ ስንሟጋት ነው የኖርነው። እንደ እሱ የአጣጣፍ ዘዬ የሚመቸኝ ቢኖር የልዕልት ጽዮን ግርማ ብዕር ነበረች።

ያው ሙግታችንም ከአቶ ወንድም ከልጅ ተክሌ ጋር ጤናም የሆነ ነበር። የሚገርመው ዛሬ ባዬሁት ጡሁፍ አንድ መሰመር ላይ ተገናኘኝ። እኔም እንደ እሱ ያለ ሃሳብ ነው ያለኝ። ስለተደረገው መልካም ነገር አመስግነን ምዕራፍ ሁለት ግን በነገር ዥዋዥዊት ሳይሆን መልክ ያለው ነገር መስራት ያለብን ይመስለኛል።

የአዲስ አበባ ባለአደራ ምክርቤት፤ ወደኢትዮጵያ ባለአደራ ምክርቤት ይደግ (ልጅ ተክሌ

ለዚህ ደግሞ እዮርም የሰማይ ምልክት ሰጥቶናል በዚሕው ቀን። መጋቢት አንድ ቀን ሁለት ሺህ አስራንድ። ዕለተ ሰንበት። ቤተመንግሥት የእስክንድርን ንቅናቄ አቅም ለመፈታተን ሲያሰላ እዮር ሉላዊውን ዓለም ያካተተ የሰማዕታት ምልክት ሰጠ። 

የተሰባሰበው የጃዋርውያኑን መንፈስ ለማደንዘዝ ነበር። የሚዲያ ባለሙያ እና የፖለቲካ ሊሂቃን ያን እንጋታለን ብለው ታድመው ነበር … ቅዱሳን ደግሞ በባልደራስ አዳራሽ…
ስለዚህ የእስክንድር ንቅናቄ መንፈስ አለው የተቀደስ። እሱን ማጥናት ያለብን ይመስለኛል። ሳናጠና ዘው ብዙም ባይረዳንም በሱ ውስጥ ያለችው ኢትዮጵያ ግን ንዑዷ ስለሆነች ለቅኖች ዳገትም ዳጥም የለበትም ብዬ አስባለሁኝ …

አሁን ግልጽ በሆነ ቋንቋ ኢትዮጵያን ኦሮማይዝድ ለማድረግ ማንፌስቶው ኦሮማማ ስለመሆኑ በሚገባ ተገልጧል በርከት ላለው ባለህሊና። ይህ ደግሞ ልብያለው የለም እንጂ በመስከረሙ ጉባኤ ወቅት ውሳኔ የተሰጠበት ነው። 

አፍሪካን በኦሮማማ እንመራለን ተብሎ። እኔም በወቅቱ ጽፌበታለሁኝ። እነ አይጠግቤ አፍሪካንም በዚህ ውሃ ቅዳ ውሃ መለስ እናጥለቀልቃልን ባዮች ናቸው። አቅሙ ከተገኜ ... በቀን ስንት ዝብርቅ መግለጫ ከማውጣት ሁለትን አካል ላንድ ጉዳይ አደራዳሪ እና ተዳራዳሪ ለማደረክ ከመብከንከን... 

ይህ የኦሮማማ መንገድ ደግሞ ኢትዮጵያ ከመፈጠሯ በኋዋላ የመጣ እንጂ ኢትዮጵያን የፈጠረ ስላልሆነ ኢትዮጵያ በተፈጠረችበት ልክ በተፈጥሯዋ ውስጥ የመምራት ጥበብ ነው የሚያስፈልጋት። ይህ ማለት ግን ኦሮማማን እንደ አንድ ትውፊት ከማዬት ውጪ 79 ብሄር እና ብሄረሰብን ይምራ ማለት ጅልነት መሆኑን አብክሬ መግለጽ እወዳለሁኝ።

 ለዛውም ሰው ተግዶሎ ተዘቅዝቆ በሚሰቀልበት ባድማ፤ ሰው ተገድሎ በሚቃጥለበት ቀዬ፤ ሰው በካንፕ እንደ እቃ ታሽጎ በርሃብ እንዲጨረስ በሚደረግበት ሁኔታ፤ የደከመን ለማገዝ የተጎዳን ለመረዳት ወንጀል ሁኖ ቀልሃ በሚያስመዝዝበት ኩነት ኦሮማማ አብነት እንዲሆን ሊፈቀድለት አይገባም። ከዚህ መንፈስ ጋር የሚያያዙ ጉዳዮች እንደ አንድ አካልነት እንጂ እንደ ህብረ ብሄር መሪነት ከታሰብ መፍትሄው አንጥሮ ወደ መጣበት መመለስ ነው።

ጠ/ሚር አብይ አህመድ የአንድ አመት ጉዞ እና ራዕይ ውጤት እና ኪሳራ መልካሙን በማስቀጠል ከአገር ኢትዮጵያ የማይመጥነው እክል በማስወገድ አዲስ መንገድ ለማስጀመር ግን በዚህ መሰል ግፋፏዊ አካሄድ የሚሆን አይደለም። ጥርት ያለ መንገድን መከተል ያስፈልግ ይመስለኛል። ለዚህ ደግሞ የእስክንድር ንቅናቄ እንደ አንደኛው መንገድ አድርጎ ማዬት የሚገባ ይመስለኛል - መልዕክቴ ለቅኖች ነው።

ግንቦት 7 ዛሬ እንዳመጥኩት ከአቶ ኤርምያስ ለገሰ ግዛታዊ ጥያቄ እንዳነሳ ተደምጧል። እንግዲህ የካድሬዎቹ ኡኡታ ዕድሉ እንዳያመልጠው ሌላ መሹለኪያ ተበጅቶለት ነው ማለት ነው። ሾልኮ መቅረቱ ጭንቅ ጥብብ የሚያደርጋቸው ስላሉ። ለነገሩ እሱ የሦስቱ የሲኦል መንገድ ታዳሚ ስለመሆኑ በአንደበቱ ነግሮናል … ያው ቁምነገር እየጣለው ሲያልፍ አባትቶ የሚያስነሳው ሃሳብ የለሽ ስለሆነ ነው። ከሞቀው መጣድ።

ቀደም ባለው ጊዜ ግንቦት 7 ሃሳብ የለውም፤ ዓላማ የለውም፤ አቅም የለውም ወጀብ ጥበቃ ነው ስንል አድማጭ አልነበረም አሁን አቅሙን የለካው ግንቦት እና ካድሬዎቹ የአብይ መንገድ ብቻ ነፍስ አድን ነው በማለት እኛ ቀድመን ስንሞግትበት የነበረውን አቅም የለሽ ስለመሆኑ ድርጅታቸው በተዛዋሪ እዬመሰከሩ ስለሆነ ክብር ለፈጠርን አንድ አምላክ ይሁን እንላልን።

እንዲያውም እንደ እኔ አሁን ላለው መሰናክል ብቻ ሳይሆን ለቀጣይም ጉዞ ግንቦት 7 ራሱን ገለል ቢያደርግ ለኢትዮጵያ መዳን ሲባል መልካም ይሆናል። እንቅፋት ነው ለመለካም ነገሮች ሁሉ። ለኢትዮጵያ እና ለኢትዮጵያዊነትም ድፍን ነው። አሁን ደግሞ በ አዲስ ኦርኬስትራ ብቅ ብሏለኝ … ግንቦት 7 ያመነ ጉም የዘገነ ብለን ስንናገር አንዲት ቅንጣትም ግድፈት የሌለበት ስለመሆኑ አሰረግጠን ነው። ቀድሞ ነገር እሱ የተጠጋው ሁሉ አይበርከትም መናድ ነው።

ወደፊትም አሁን መሰረትኩት በሚለው የግጥምጥም ጉዳይ ሲተረተር ነገር ይታያል። ጠብቁት። በህይወቴ ሙሉ እንዲህ ዓይነት አይበርክቴ፤ አይጸኔ መንፈስ አይቼም ሰምቼም አላውቅም። ለስኬትም አልታደለም … 

በዬዘመኑ ሲንጠባጠብ ትውልድ እንዲሁ ስለሱ ይታረዳል … ይባክናል፤ መቅኖ ያጣል፤ አሁን ደግሞ በአዲስ ዜማ አዲስ ትወና አዲስ አባባ ላይ ተደንቅሯል። መስከረም ላይ ስለሱ የተሰዉት 5  የአዲስ አበባ ሰማዕታት ጉዳዮቹ አይደሉም 

… ሌላ ደም ደግሞ ጠምቶታል … ያነን ያነፈንፋል … ይህቺንም ጠጋ ጠጋ ያለው የ አብን ጉልበት፤ የባልደራስ ንቅናቄ አስግቶት ነው። እንጂ እሱማ ሦስት ቀን ቤተ መንግሥት ተምኒልክ፤ ሁለት ቀን ተናዝሬት / አዳማ/ ቤተ መንግሥት፤ አንድ ቀን ተታከለ ቤተመንግሥት ውሎውም አዳሩም ተዚያ ነው … ያው ለ እንቅፋት የተፈጠረ አይደለ የጉሮሮ አጥንት፤ አደናግሬ እና አምታቴ ስለሆነ አሁን ደግሞ በአዲስ ጃኬት …
  
/ ብርሃኑ፤ ኦዲፒ እና አዴፓ (ሚኪይ አምሃራ)

የብዙ ቤት የብዙ መንፈስ አፍራሽ እና ናጂም ስለሆነ ይህን መሰል ማነኮር ተፈጥሮው ነው። እሱም አይበረከት የተጠጋውም በርክቶ አይተን አናውቅምና። ሁልጊዜ የጉሮሮ አጥንት ነው ለኢትዮጵያ የነፃነት ተገድሎ። 

ባለአደራ ምናምን የሚባለው ነገር ለኔ ትክክል አይመስለኝም/ ብርሃኑ ነጋ
<<ባለአደራ ምናምን የሚባለው ነገር ለኔ ትክክል አይመስለኝም። አቶ ታከለ ይሄን የማሸጋገር ሂደት በሚመለከት በትክክል ያልሰራው ነገር አለ ከተባለ ሂስ ማቅረብ ጥሩ ነው።>>/ ብርሃኑ ነጋ
እና ቢበቃው በአክብሮት እንጠይቃለን፤ ይልቅ አዲስ ዶክተሪን አምጥቷል ዝልብ ነገር አቅሙን በዚህ መለካት ይቻላል፤ ስለምን እንደሚታገልም ራሱም አያውቀውም። መቼም እንደ ግንቦት 7 ያለ አድካሚ ድርጅት የለም።  የሚያሳዝኑኝ ይህን ዓላማ፤ ሃሳብ፤ ራእይ የሌለው መንፈስ እንደ ጣዖት የሚያመልኩት ቅኖች ነው። በቃ ለሥልጣ ካልሆነ ስለምን በዬዘመኑ በአዲስ ሥያሜ ትውልድ ያባክናል? መላ ቢስ።

ፖለቲካ የስልጣን ጉዳይ አይደለም - / ብርሃኑ ነጋ | Ethiopia
Published on Mar 30, 2019

… ፈርሷል ስለሚበለው አልፈረሰም ጭንቅላቱ እያለ መፈረስ አይታሰብም፤ በአዲስ አድቅቅ ስልት እና ስትራቴጅ ነው እንደ ብአዴን ሥሙን ቀይሮ ብቅ ያለው … ለዛውም ለዲያስፖራው ፓለቲካ እና ለ ኦሮማማ በሚመች መልኩ ሁለት መንታ ሃሳብን ይዞ ..
  
አውራው ድርጅት ኦዴፓም ቢሆን እኔ ፓርቲ ነው ብዬ አልቀበለውም፤ ኦሮማማውን ለራሱ ተሸክሞ እኛን ለቀቅ ማድረግ ይኖርበታል። 

ነፍሱ ያለችው ከነቀምት፤ ከአሰላ፤ ከናዝሬት፤ ከደብረዘይት፤ ከሻሸመኔ፤ ከጅማ አይደለም ነፍሱ ያለችው ከአዲስ አበባ ነው ሁሉ አማረኝ ስለሆነ፤ መቼም አዲስ አባባ ላይ ነዳጅ የወጣ ያህል ሰፍ ብሏል እሰከ ቅል ቋንቁራው።  

ጀግኖቹ የቆረቆሩትን ያሳደጓቸውን ከተሞችማ እሱ ከተረከበበት ጊዜ ጀምሮ እነዚህን ከቶሞችማ አድቅቆ አንኩቷቸዋል የነፍጠኛ እያለ። ይህን እንኳን በቅጡ መበለት አቅቶ ነው በግፋፎ ሃሳብ በመራኮት ላይ ያለነው።

በቅድሚያ ስለምን ድሬድዋ እና አዲስ አባባ የጠ/ሚሩ የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ተነፈጋቸው ብሎ ከዛ መነሳት ያስፈልጋል። ከዚህ ላይ የተጠመደ ፈንጅ ስላለ ነው። ከሁለቱም ከተሞች። ስንት ማሞ ቂሉ እንዳለ ቢነግሩን ጠ/ሚር አብይ አህመድ መልካም በሆነ ነበር። „አዲስ አባባ እንደሌላው ከተማ ናት“ ይሉናል።

በየትኛው ቋንቋ ይሆን እዬነገሩን ያሉ? ደግሞ ሰለ አፍ መፍቻ ቋንቋችን ተርጓሚ ሊያስፈልገን ይሆን? ሰውን በጣም አጃጅሎ ማዬትን የመሰለ ኪሳራ የለም። አዲስ አባባ ከሌላው ከተማ በፍጹም ሁኔታ የተለዬች ናት። አይደለም ከኢትዮጵያ ከተሞች ከአፍሪካም የተለዬች ናት። ልክ እንደ ኒዎርክ እና እንደ ጄኔባ የምትታይ ከተማ ናት። እና ጅላጅሉን ግፋፎውን ይፈልጉ አዲስ እንደፈጠሩት ካድሬ እንደጦማሪ አቶ ስዩም ተሾመ …

/ / አብይ አህመድ በወቅታዊ ሀገራዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሰጡትን ሙሉ ጋዜጣዊ መግለጫ ይከታተሉ


ስለ አቶ ስዩም ተሾመ ጽፌ ቀደም ብዬ የትዝብቴን ቋት በዝርዘር ገልጬ ነበር። ከሳቸው ጹሑፍ ማግስት ስለሚከተሉት ጉዳዮች ከጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ ጋር በነበረው ቆይታ ክንክን ስላደረጋቸው የውሃ ፖለቲካ አንስተው ጋዜጠኛ እስክንድርን ሞግተው ነበር።
ውሃም የሜንጫ ቤተኛ.

የውሃ ፖለቲካ ስለሚያብከነክናቸው ቆሞስ ኢንጂነር ስመኘውን ለሞት ዋዜማ መረጃ አቀባይ እንደነበሩ እናስታውሳለን … ሰሞኑም አዲስዬ በውሃ ለመቅጣት አንድ ሙከራ ተደርጎ ነበር። እሳቸው መብረቅ ናቸው ለኢትዮጵያ ፖለቲካ። በዬዘመኑ ይህም መሰል ጉድ የተላቡሰ አይጠፉም። እነ አቶ ይገርም አለሙ፤ እነ ሰዓሊ አምሳሉን ማሰብ ይቻላል። በዘመነ ህወሃት የነበሩ ተከፋዮች አሁን የሉም። አሁን ደግሞ የኦርማማ ጠሐፊወች ናቸው ያሉት …   

አሁን ደግሞ አዲስ አባባ እውሃ ከኦሮምያ ነውና የምታገኘው ዋጋ ትክፈል ያሉትን ጠ/ሚር አብይ አህመድ ይኸውን የውሃ ፖለቲካ በሚገባ ሂደውበታል … አንግዲህ መቀሌም ለጣና መክፈል አለባት ነው በዚህ ዕሳቤ። የነገው የአባይ ግድብ ህልምንም ከዚኸው ጋር አይተን ከምንጩ ከአማራ መሬት ላይ ስለሆነ ለዛም ግብር ይክፈል ኦሮምያን አክሎ ሌሎችም ክልሎች ማለት ነው …

"በመሆኑም ማደናገሪያ መፈለግ አስፈለጋቸው። ሴራ መሸረብ አማራጭ የሌለው አማራጭ ሆነ። ከዛሬው ሴራዎች መካከል አንደኛው Seyoum Teshome በኩል የተለቀቀው ነው። ስዩም በየዋህነት ሰተት ብሎ ለሴራቸው ተጋላጭ ሆኗል።"

የሆነ ሆኖ ጦማሪ አቶ ስዩም መስፍን የሰሞኑ የግዞት ፖለቲካ በቤተ መንግሥት የተመሰጠረውንም አጋርተዋል … የባልደራስን ንቅናቄ አግቶ በቤተ መንግሥት ለመጠርነፍ ስላለው ምናምንቴ … ግራጫማው የጠ/ሚር ባለማስቲካ የፕሬስ ሰክራትርያት ቢሮ አቶ ንጉሡ ጥላሁን ከአቶ ጀዋር ጋር ወጥ አቋም አሳልፈዋል።

ለነገሩ በሰሞናቱ የጠ/ሚር አብይ አህመድ ጋዜጣዊ መግለጫ ያው የፕሬስ ቢሮውንም በመተካካት አስኪዶታል። አቅመ ቢስ ስለመሆኑ አውጇል። እኛም ተዚህ ሆነን ነፍሱን አያማራው ብለናል … ከነገረ ጃዋርውያን ግጥም ስለሌን … ያው ፍደኛው አማራ ክልል ግን እንደጣለበት ይሸከመው ዬዘመኑን ቅርፊት እና የምድር እንቧይ … ውክልናው ተዛ ነው የተገኘው አይደል … ታሪሰኛ ቢሆን ወይ ደቡብኛ ቢሆን መልካም ነገር በሆነ ነበር …
  
የሆነ ሆኖ አንዱ ማገቻ አዳራሽ ሲያሰናዳ ሌላው ደግሞ አብሬ ነኝ የሚል ሌላ ማምታቻ ጉዳይ ይዞ ብቅ ብሏል። የጃዋርውያን መንግሥት አሁን ውጥረቱን ለማርገብ በግራ በቀኝ እዬተጣደፈ ነው። የእኔም ህልም ወንበሩ ባዶ መሆኑ ምስክርንት እያገኜ ነው

 ..የጠ/ሚር አብይ ብትክትክ አቋም ማዕቀቡ እና ውስጣቸው በሚፈጥረው ግጭት መስመር አስይዞ በተሰጠው ቀጭን ትእዛዝ መሰረት መልክ ለማስያዝ እንቅልፍ አጥቷል፤ ወይ ቤተሰቡን ወይ ራሱን ያጣታል … በዚህ ውስጥ አላዛሯ ኢትዮጵያ በታፈነ ፍላጎት ፍዳዋን ታያለች … ድንብልብል ክዝን መከራ ላይ ናት እናት አገር ኢትዮጵያ፤ ካዝናው መሟጠጡን በሸኘው ሳምንት ላይ አድመጠናል … ግብዣው፤ ሆቴል ኪራይ እዬተከፈለላቸው የሚዘማነኑት ቅልቦች ዓመት ሙሉ ፈረነሹ … ህም! አማካሪዎችም በዶላር ክፍያ እንዳላቸው እዬተደመጠ ነው … ቀልድ እና ክምሩ ተዚህ እና ተዚያ ማዶ በወጀብ እነሆ ይናጣል … 
   
ምልስት ይሁም እስኪ ወደ ቀደመው …. እንደ እኔ እኒህ ሰው የጠ/ሚሩ የሚስጢር እርካብ ባለሙሉ አንባሳደር መሆናቸው ይሰመረበት ማለት ነው አቶ ስዩም ተሾመ ማለት ነው። ይልቅ አንድ አለስልሴ ከጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው „የዋህ“ የሚለው አገላለጽ ቢመረመር እንመክራለን።

የአዲስ አበባ ጉዳይ ለእነ ዐቢይ መንግስት የእግር ሳት ሆኗልጌታቸው ሽፈራው

አቶ ስዩም ተሾመም የኦሮማማ ቤተሰብ ብቻ ሳይሆኑ፤ እዬተከፈላቸው ከመቅድም እስከ ዛሬ ሰፊ ግልጋሎት የሚሰጡ የሰውሩ የመንግሥት አንደበት ስለመሆናቸው ማስታወስ እሻለሁኝ … አቅጣጫ አስቀያሽ ዕጸ በለስም ናቸው።
  
ግፋፎ ተሸከምን፤ ግፋፎ እና ጥራኝ ብለን፤ ግፋፎን የሙጥኝ ብለን፤ ግፋፎን ነፍስ አባት አድርገን፤ ግፋፎን ምህንድስና አድርገን፤ ግፋፎን ቀድስን፤ ግፋፎን ወርበን፤ ግፋፎን ማህሌት አስቁመን፤ ግፋፎን ተቃቅፈን፤ ግፋፎም ማጫ አማተን፤ ግፋፎን አጊጠን፤ ግፋፎን ቆንድለን፤ ግፋፎን በዲላታ ድረን ኩለን፤ የግፋፎ መልስ እና ቅልቅል ደልቀን፤ የግፋፎን ሰፈፍ ምጥጥ አድርግን ጨልጠን እንጣፍጣፊ ሳናስቀር ሟጥጠን፤ የግፋፎን ሰብል በህሊና ጎታ አካተን ወደዬት ? መመለስ ነው አቅም ያለው።

ያ ኦሮምያ ላይ ባለቤትነቴ የሚረጋገጠው አዲስ አባባ ላይም ያሉት የዶር ለማ መገርሳ አዘለኝ አዚምም ስለመሆኑ በቀለም ይጠፍልኝ፤ ታቦቱ ይቀረጽልኝ ያሉት የዶር ለማ መገርሳ ንግግር እንደ ቁምነገር ተወስዶ እሱንም እናንግሥ ሲባል ግፋፎ ሰርግ ቢጠራ፤ ግፋፎ ለግብር እልፍኝ ቢያስከለክል የተገባ ነው እንላለን …

የሆነ ሆኖ እኔም ትናንት ያልኩት ነገር ስለነበረ …  አደዛንዥ ዕጹ አዚም ቢለቀን …እስኪ ደግመን ደጋግመን እንመርምረው …  ሰው ገድሎ ዘቅዝቆ መስቀል፤ ገድሎ ማቃጣል፤ የቡራዩ እና የጌዲኦ ማሳካር ካልሰከርን በሰተቀር አዳኝ አደርጎ መውሰድ እብደት ይመሰለኛል።

የዶር ለማ መገርሳ ንግግር እና ዕድምታ ...ው።


ኢትዮጵያዊነት ተፈናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጢር!

የኔዎቹ ኑሩልኝ።

መሸቢያ ጊዜ።  

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።