ልጥፎች

ኡኡ የአድማጭ ያለህ! ሰሚ ቢገኝ!

ምስል
ማመዛዘን - ማገናዘብ - ማያያዝ - ማወራረስ - መመርምር - አቅጣጫን ማወቅ። „በዬሰባቱ ዓመት መጨረሻ የዕዳ ምሕረት ታደርጋለህ።“ ኦሪት ዘዳግም ምዕራፍ ፲፭ ቁጥር ፩ ዕንባ በጣምራ ኢትዮጵያ ላይ በተደሞ ቀጥሏል .. ወንበሩ ባዶ ነው ... . ከሥርጉተ© ሥላሴ 16.08.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ ከሰሞናቱ „አክ ወሬዎች“ የሚል ከሊቀ - ሊቃውነቱ የፕ/ሃይለማርያም አለማርያም አንድ ጠንከር ያለ ጹሁፍ ቀርቧል። አታሟርቱባቸው ዓይነት ነው። የሊቀሊቃውነቱ ቅንነቱ ብቻ ሳይሆን ንጹሁ የሆነ መንፈሱ ይመርካል ውስጣቸው ንዑድ እንደሆነ ያመለክታል። ግን የሆነውን ነገር ግን፤ በመሆን ላይ ያለውን ነገር ግን ... አልዳሰሰውም ..   አብሶ ፕሮፌሰሩ የዶር አብይ አህመድን የብፁዕን አበውን  ጉቡኝት መንፈሱን በማዬት ሙሉ ለሙሉ ዶር አብይ አህመድ  ደህና መሆናቸውን በሥራ ብዛት እንደ ተሰወሩ ነው ያመኑት። አብይ ምንም አልሆነም ነው የሚሉት። እንዲያውም በዚህ ዙሪያ የሳሳበቸው ወገኖችን ያልተገባ መስዋዕትነት አድርገው ነው ያዩት፤ እንደ አፋቸው ቢሆን መልካም በሆነ ነበር። ግን የሆነው፤ በመሆን ያለው ነገር እሳቸው እንዳሰቡት አይደልም። በሳቸው ምትክ የተወከሉት ለጊዜው ዶር ሙላቱ ተሾመ ናቸው። በማዕካለዊ መንግሥት ደረጃ በተጠሪነት ሁለቱንም በአማካይ በፊርማ እዬከወኑ የሚገኙት። እርግጥ ነው ዶር አብይ አህመድ በድሮው አቅማቸው በመንፈስ ነፃነት ያወጧቸው ቃሎች በሙሉ ሙሉ ለሙሉ አብይ ከእነ ሙሉ ነፃነቱ ለማለት ያስደፍራል። ያ ያስደሰተኝ ለእኔ እንደገና የመወለድ ያህል ነው። ያ የሆነው ግን አዌርነሱ ስለጠነከረ ነው፤ ለማዘናጊያ፤ ትጥቅ ለማስፈታት ነው።  እኔ እንደ ማስበው ከዚህ ጉዳይ ጋር አንድ ግዙፍ መሰረታዊ

የእቅፋት እንቅፋት፤

ምስል
በነገ እና በእኛ፤ በዛሬ እና  በእኛ መሃከል ምን ይደረግ? ደግሞስ ከቀናቶቹ ጋር ምን እና ምን ነን? „አቤቱ እንደ ቸርነትህ መጠን ማረኝ  እንደ ምሕረትህም ብዛት መተላለፌን ደምስስ።“ መዝመረ ዳዊት ምዕራፍ  ፶ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ  © ሥላሴ  15.08.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ ·       እ ፍታ። መንግሥት ህዝብን ቢጨፈጭፍ ይውርዳል። ህዝብ ህዝብን ቢጨፈጭፍ ግን እንዴት ይኮናል። አሁን ያለው እንዲህ ነው። አንዱ ህዝብ አቅም ካለው ሌላውን መጨፍጨፍ፤ ማፈናቀል። አፈናቃዩ ደጋፊው ክፉ ህሊና ነው።  በልጅነቴ ዝምተኛው አባቴ አበይ ነፍሱን ይማርልኝ እና ዝምታውን ጥሶ የሚያልፍ እንጉርጉሮ ነበረው „እናት አባት ሲሞት በአገር ይለቀሳል፤ እህት ወንድም ሲሞት በአገር ይለቀሳል፤ አክስት አጎት ሲሞት በአገር ይለቀሳል አገር የሞተ እንደሆ ወዴት ይደረሳል“ አሁን ያለው ጣምራ ዘመቻ የታቀደው የሽግግር መንግሥትን ወይንም የተጽዕኖ ፈጣሪዎች መንግሥት ስኬታማ የሚያደርግ እድምታ ነው ያለው። ተፎካካሪዎችም መሬት ላይ ሥራ ለመጀመር ያልፍለጉበትም ምክንያት ያ ነው። የሚጠብቁት ህልም ስላላቸው። በመሃል ግን ስለ እነሱም ህይወት ምን ያህል እርግጠኛ እንደሆኑ አይታወቅም?  ·       መ ህበረ ቤት።  አገር ማለት በሥርጉትሻ ዕይታ ዓለም አቀፍ  እውቅና ባለው መሬት   እና ካለካሰማ በሚኖር ሰማይ ሥር የሰዎች ማህበረ - ቤት ማለት ነው። ማህረ - ቤቱ ውስጥ የሚኖሩ አባልተኞች ከተጨራረሱ አገር የሚባለው ነገር አይኖርም። ችሎ የኖረው ምንጃር ደግሞ አሁን ተነስቷል። ባለለቀው ሳምንትም ስለ ሰላሌም ዜና ነበር።  „ ብፈልግ ኦሮሚያን ከአራት ወር በ

ተጠዬቂ እስኪ አንቺ መከረኛ!

ምስል
መርዝ እዬተዘራ መርዝን ማምከን አይቻልም። „ነገር ግን ወረተኛ ለጥቂት ቀን የሚሆን ወዳጅ አለና በመከራህም  ጊዜ ካንተ ጋር መከራህን ከአንተ ጋር አይታገሥም እና  ፈጽመህ አትመነው“ ምዕራፍ ፮ ቁጥር  ፲ ከሥርጉተ© ሥላሴ 15.08.2018  ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ሰው መሆን ሰው ሆኖ መፈጠር ብቻ አይደለም። ስለ ሰው መፈጠርም ዕውቀት ሊኖር ግድ ይላል። ሰው መሆን ቢያንስ ከእንሰሳ መለዬት ማለት ነው በቀላል ትርጉሙ። ሰውነት ለኢትዮጵውያን ከሁሉም በላይ የላቀ ሃይማኖታዊም ዶግማም ነበር። እግዚአብሄር ሰውን ቤተ መቅደሱ አድርጎ ፈጠረ ከሚል ሃይማኖታዊ ዶግማም ጋር የሚያያዝ „ ሰውን እንደ መልካችን በአምሳላችን አንፍጠር“ አሁን ግን እኔ ሰው አይደለሁም እያልን ነው። ሰው መሆን ስለሰው መጨነቅ መሆን ቀርቶ ስለሰው እንዴት እንደሚገደል፤ እንዴት እንደሚወገድ፤ እንዴት እንደሚገለል፤ እንዴት እንደሚታረድ፤ እንዴት አካሉ እንደሚጎድል፤ እንዴት ሥነ - ልቦናው እንደሚሸነሸን፤ እንዴት የውስጥ ሰላሙ እንደሚታወክ መራቀቅ ሆኗል ጀግንነቱ። ጀግንነት ሰብዕናን ሰው መሆንን ጥላህ ከወገብ በላይ ሰው ከወገብ በታች ጭካኔ፤ ወይንም ከወገብ በላይ እንሰሳ ከወገብ በታች ሰው ሆነህ በጥምር መንፈስ በደመ ነፍስ መነዳት ሆኗል። ሰው በራሱ ኢጎ ሠረገላ እዬገላበ ብቻ በቻቻታ እና በሁካት፤ በኳኳቴ እና በዲልቃ መንገድ ሆኗል የሰውነት ደረጃው። በአደባባይ ሰው ሰው መሆን አቅቶት፤ ስለሰው ሰብዕና ማሰብ ተስኖት ጭካኔን ት/ ቤት ከፍታችሁ ልጆቻችሁን አስተምሩ፤ አረመኔነት የልጆቻችሁ መለያ ምልክት የሰብዕናውም መፈጠሪያ አስኳል ይሁን እዬተባለ ነው፤ ለሽብርተኝነት ካሪክለም ይዘጋጅ እዬተባለ ነው፤ ማፍርስ፤ ማቃጠል እንደ ክብር እንደ ሞራል ልእ

የጉድ ዘመን - የመርዝ ናፍቆት።

ምስል
እርጋሞት አለመባልህ ስለምን? „እዬሱስ ግን ህፃናትን ወደ እርሱ ጠርቶ፣ --- ህፃናት ወደ እኔ ይመጡ ዘንድ አትከልክሏቸው፤ የእግዚአብሄር መንግሥት እንደ እነዚህ ላሉት ናትና። እውነት እላችኋለሁ፤ የእግዚአብሄርን መንግሥት እንደ ሕፃን የማይቀባላት ሁሉ ከቶ አይገባባትም አለ።“   ሉቃስ ምዕራፍ  ፲፰ ከቁጥር ፲፮ እስከ ፲፯ ከሥርጉተ ©ሥላሴ 15.08.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ። ይድረስ ለአብን ባህርዳር። ·       መነ ሻ። https://youtuby.xyz/watch?v=FhDm_XoagSw ሄኖክ የሺጥላ ለጀዋር ወቅታዊ ንግግሮች የሰጠው መልስ አልፎ አልፎ ሰዎች ምን ያስባሉ ስል አንዳንድ ነገሮችን እከታተላለሁኝ። ዛሬ ያው አቶ ይቱብ አንድ ክሊፕ አመጣልኝ እና አዳምጠኩት። ስንት ግራሞት እንዳለ፤ ስንት ትከዜ እንዳለ፤ ስንት የውስጥ ሃዘን እንዳለ፤ ስንት ሰቀቀን እንዳለ ቤቱ ይቁጠረው። ደስታችን ከቅጽበት ያለፈበትን ጊዜ አላስታውሰውም። የሻሸመኔው ሰቀቀን እህል ውሃ ጋር አጣልቶን አይናችን እንዳፈጠጠ እያሰደረን፤ ደግሞ ቀጣዩ የት ቦታ ቃጣሎ፤ የት ቦታ መፈናቀል፤ የት ቦታ የሰው እርድ እናዳምጥ ይሆን እያልን ሌቱም ቀኑም ተደባልቆብን ጭንቅ የሚለን ስደተኞች አለን። የድምጽ አልባዎች እናቶች አጀንዳኛ። ሁለት ነገር ብቻ ላንሳ ወጣት አቶ ሄኖክ የሽጥላ ካነሳው። ግን የጤና ነው ለማለት በፍጹም አልደፍርም። አንደኛው የጎንደር ህብረትን በሚመለከት ነው እኔም የምስማማበት ነው። የማንነት ቀውስ እንደ ሳጅን በረከት ያለባቸው አማራን ደግሞ ሌላ 43 ዓመት ለመቀብር የተነሳ መንፈስ ነው። አሁን ወጣቱ ትውልድ በጅ የሚልም አይደለም ጥሏቸውም ሄዷልም። አንሱ እዛው የዛሬ 43 ዓመት ላይ እንደ ኩሬ ውሃ