ልጥፎች

የሥልጣኔ ድንጋጌ ጥሩ ዜና በበተልሄም ብሥራት ሲሰክን!

ምስል
የማግስት ብሥራት ድንጋጌ ናት የፈጠራ ባለቤቷ ወጣት ቤተልሄም ደሴ። „ሁሉም በመቅደሱ ምስጋና ይላል።“  መዝሙር ፳፰ ቁጥር ፱ ከሥርጉተ©ሥላሴ 19.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።፡ ማስተዋሏ የበረከተ ነው። ቅኝቷ ለምለማዊ ነው። እረቀቷ እዬራዊ ነው። በዓላማው ውስጥ ከዕድሜዋ በላይ የሚጠይቀውን ትዕግስት ተጎናጽፋ በአማኑኤል ተሰጥቷትም ሐሤትን በተሟላ ተስፋ በገፍ አጋርታናለች። ብርክታዊት! ለኢትዮጵያ አገሬ ሽልማትም ናት። እሷም ደስተኛ ናት። እውነት በማይመስሉ የኮንፒተር ሳይንስ ፍልስፍናዎች እና ውጤቶች ተሰማርታ ስኬታማ ሆናለች። ዕድሜዋን ሳያስቡ ተግባሯን ብቻ ማሰቡ ብቻ ይሻላል። ዕድሜዋን አስበው የህይወት ጊዜዋን ሲያስተውሉ ልበወለድ ስለሚመስል። „ለእግዚአንሄር ግን የሚሳነው የለም“ ማለቱ ለአማንያን ታምራቱን ያይ ዘንድ የሆነው ሁሉ እንዲህም ሆነው። ብሩሕ ቢዥነር ናት። እማጅነሽኗ እርቀቱ ይገርማል። የምትገርም ዕንቡጥ ቀንበጥ ፈላስፋ ወጣት ናት። ለ21ኛው ምዕት የተፈቀደላት ባለመክሊት ናት። እውነትም ቤተልሄም የዬምስራች ዓውደ ምህረት የሥልጣኔም ጥሩ ዜና።   የሚገርመው በዚህ ዕድሜዋ ልዑል እግዚአብሄር እኛን የሰጠበት ሚስጥር ደርሳበታለች። አትጨናነቅም፤ መጨናናቅንም አጀንዳዋ አለደረገችውም። ብሩሁን ጭንቅላቷን ማበከን አትፈቅድም እና። ጊዜዋን ባልባሌ ጉዳያዎች አታሳልፈም። ጌዜ ወርቅ ነው ገቢር ላይ ውሏል። ደስታ ተስጥዖችን ስለመሆኑ እዬኖረችበት ነው። ህይወትን ቀለል ዘና አድርጎ መኖርንም በዚህ ዕድሜዋ ታስተምረናለች። ፍልቅልቅ ያለች፤ ቀለል ያለች ቁጥብ ወጣት ብርሃን ጠገብ ወጣት ናት። የተስፋ ውሃ ልክ ንጥረ ነገር እርጋታዋ የችግር መፍቻ በእጇ ስላለ ብቻ ሳይሆን ኢማጅኔሽኗ

ዘመን ያልፈታው እንቆቅልሽ፤ እኮ ምን ሳውቅልህ።

ምስል
  ዶር አንባቸው   መኮነን አደራ ተብልቶ፤ ቃልኪዳን ታጥፎ ተንሳፋፊ በግለት፤ አቶ አሚር አማን የጤና ጥበቃ ሚ/ር ቀጣይ በክብር።                                                               ዘመን ያልፈታው እንቆቅልሽ፤                  እኮ ምን ሳውቅልህ?

የምናከብርህ ዶር አንባቸው መኮነን ከጎንህ ነን!

ምስል
እንኳን ደስ አለህ አዴፓ¡ „ለቅዱሳን ሁሉ ይህች ክብር ናት።“ መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፻፵፱ ቁጥር ፱ ከሥርጉተ©ሥላሴ 18.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ                                                                      ·       እ ፍታ። የኔዎቹ እንዴት ናችሁ፤ ብዙ ሰው ሹመቱ የራሳቸው ነው እኛን ምን አገባን የሚሉ አሉ አሁን እኮ መንግሥት አለ ብለን ስለምናምን እንጂ እኔ አዲትም ቀን በሹመቶቻቸው ዙሪያ ጽፌም አላውቅም፤ ፓርላማም ጉባኤውን በትጋት እማዳምጠው ከመጋቢት 24 ቀን ጀምሮ ነው።  ሌአለው ቀርቶ እዚህ ሲዊዘርላንድ ማን አንባሳደር እንደሆነ፤ አንባሲው ቢሮው አድራሻው የት እንደሚገኝ ሁሉ አላውቀውም፤ ምን ይዶለኛል፤ ምንስ ያገበኛል፤ እኔ ዜጋ አይደለሁምና። አሁን አስተያዬት የምንሰጠው የ እኔ ከማለት ነው እንጂ ይህን ራሱን አይተን አይተን እናቆመዋለን። እኔ በተለይ ወንበሩ ባዶ ሆኖ ስላዬሁት ብቻ ሳይሆን ከስሜን አሜሪካ መልስ ጠ/ ሚሩን የማስወገድ አደጋም ተደርጓል ብዬ አስባለሁኝ፤ ምክንያቱም አብዩን አሜኑን እጅግ አቅርቤ አዬ ስለነበር ፈጣሪ መልዕክት ልኮልኛል ብዬ አምናለሁኝ። ያ ሳይሳካ ሲቀርም እገዳ ማዕቀብ፤ ቅደመ ሁኔታ ተቀምጧል ብዬ ስለማስብ አሁን እዬሆነ ያለው ነገር ብዙም አልደነገጥበትም። እኛ ነው እየሠራን ያለነው እያለን ነው አቶ ጃዋር መሃመድ፤ ሌላው ቀርቶ የሱማሌ ችግር እኛው ነው የፈተናው፤ ኢትዮጵያ ያለው ስታዲዬም እኔን ደግፎ የሚወጣው ህዝብ ስለማይችለው ለዚህም ነው ከሰው ጋር መገናኘቱን ያቆምኩት እዬተባልን ነው፤ በሌላ በኩል ተበክሮ የሚነገረው እጅግ አስፈላጊ ሰው ስለሆነ ለህይወቱ ጠንቃቃ መሆን እንዳለበት ምክር እንደሚሰጠውም ገልፆ

አቶ ታገሰ ጫፎ አፈ ጉባኤ ሆኑ።

ምስል
አቶ ታገሰ ጫፎ አፈ ጉባኤ ሆኑ። „ሳሙኤልም ወደ አምልኮቱ መለሳቸው፤ የልቦናቸውም ዓይኖች በሩላቸው።“ መጽሐፈ ሄኖክ ምዕራፍ ፴፫ ቊጥር ፶፬ ከሥርጉተ©ሥላሴ  18.102018  ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። አቶ ታገሰ ጫፎ ክብርት ወ/ሮ ሙፍርያት ካሜልን ተክተው አሁን በሙሉ ድምጽ ካለ ሌላ እጬ ተዋዳዳሪ የኢትዮጵያ ፓርላማ እንደመረጣቸው አየሁኝ። በሰሞናቱ ስብሰባ ከፓርላማ ተሳታፊዎቹ በሚቀርበው ጥያቄ ላይም ማብራሪያ ሲሰጡ አዳምጬ ነበር።  የሆነ ሆኖ ያው ሌላ እጩ የለም፤ ተቃውሞ የለም። ድምጸ ተዕቅቦ የለም። እንግዲህ አቶ ታዳሰ ጫፎ በዘመነ ወያኔ መራሹ ግንባር በኢህአዴግ ከሥር ጀምሮ በተለያዩ የሃላፊነት ቦታዎች አብሮ የኖሩ፤ በድርጅታዊ ህይወት የበቀሉ፤ በቀለም ትምህርትም የገፉ፤ ስለሆናቸው የህይወት ታሪካቸው ሲገለጥ ሰምቻለሁኝ ቀደም ባሉ ቃለ ምልልሶችም መጠነኛ መረጃ አለኝ። በሙሉ ዕድሜ ላይ ስለሚገኙ የተገባ ነው ባይ ነኝ። ታሪካቸውን ጠለቅ ብዬ አላውቀውም። የገረመኝ የፓርላማው ጉዳይ ነው። የቀረበለትን ምግብ ሳያማርጥ መዋጥ ብቻ ነው የማህያው ውል። የተሻለው መስሎኝ ነበር ግን ያው ዴሞክራሲያዊ ማዕክላዊነት የሚባለው ፈሊጥ አሁን እዬሠራ ስለመሆኑ በዬስብሰባዎቹ እያስተዋልኩኝ ነው። 100/100 ህም? መቼም በ2010 የተጀመረው የስብሰባ ዘመን ለ2011 አጋብቶበታል። መደበኛ ስብሰባዎችን ማለቴ ግን አይደለም። የሆነ ሆኖ ምን ተሰማሽ በአቶ ታገሰ ጫፎ ብባል ጥሩ ስሜት ተሰምቶኛል።   እኔ አቶ ንጉሡ ጥላሁን የአቶ ጃዋር አህመድ፤ ብቻ ሳይሆን የኦህዴድም  ቀዳሚ ምርጫ ስለሆነ ያ ሪኮምንዴሽን እና ለሳቸው የሚሰጠው ነጥሎ ከአማራ ክልል የማቅረብ፤ የመንከባከብ እና ወኪላችን፤ ጭንቅላታችን ነው ብሎ ኦዴ

እኮሳ!

ምስል
እኮሳ ! ወደ ዬት ? „ከሱም የተነሳ ባንደበቴ ነገር ተነገረ፤ ምድርም ጠፋች ብዬም እጮኽ ነበር።“   መጽሐፈ ሄኖክ ምዕራፍ ፳፱ ቁጥር ፯ ከሥርጉተ © ሥላሴ 17.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ የራስ ተሰማ ናደው ቅኝተኛ ቀኝ ጌታዎቻችን። ·        እኮሳ!  ወደ ዬት ጥሩ ጥያቄ ነው። አሁን በምናዬቸው ምስቅልቅሎች አንዳንድ ጊዜ ድንጋጤ እንዳንድ ጊዜ ብስጨት፤ አንዳንድ ጊዜ ሀዘን ይሰማናል። ስለምን ቢባል አዲስ ሥርዓት ለመፍጠር ያለን ተስፋ እና ጭብጡ የሚነግረን ድብልቅልቅ፤ ውልቅልለቅ ያለ ድንገቴ መረጃ መላ ከማጣቱ የተነሳ ነው። ብዙ ነገሮች ዝንቅ ናቸው። የእነኝህ ቀውሶች መነሻ ያው የራስ ተሰማ ናደው የሴራ ምህዋር ሲሆን ነጠል አድርገን ለማዬት ግን እኔን በሚገባኝ ልክ ትንሽ ልፈትሽው። ለነገሩ እኔ ከሰሜን አሜሪካ ጉዞ መልስ የሆነው በአባ ዝምታ የሐምሌ ዕድምታ ብዙ ኮልሚያለሁኝ። አማራን በተመለከት ምንግዜም ያው ነው። ብዙም አልጠበቀነም ባልጠበቀነው ልክ የሆነውን ከዕለቱ ጀመርነን ታዝበናል። አንቦ ይናገር! ግን ዛሬም ትንሽ በተያያዘ መልኩ ልበል፤ ቀውሰኞች በጅረታቸው እስኪ ይፈተሽ … ·        ቀድሞውንም የወያኔን ዓላማ ሲያራምዱ የነበሩ ግን ተጋሩ ያልሆኑ በፍጹም ሁኔታ የአብይን መንፈስ የማይፈቅዱ አሉ። እንደ አቶ ሽፈራው ሽጉጤ አይነት እነኝህ ከአኩራፊው ማህበር መዶል እንችላለን።   ·        በፍጹም ሁኔታ ከአብዮታዊ ዴሞክራሲ ውጪ መሽቶ የማይነጋ የሚመስላቸው አሉ ማህበረ ተጋሩ ብቻ ሳይሆን የማህበረ ተጋሩን ስሜት የሚጋሩ። እንደ ሳጅን በረከት ስምዖን አይነት። ·        በዛ በሽግግር ዘመን አብረው ሆነው