ልጥፎች

የምዕት ፈርጧን አርቲስት ኢፋ /ኢቢታ/ ፔሩን "በተባረከች አገር ለተባረከ ትወልድ" ተስፋ ውስጥ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ለውጡ እንደ ዝናሽ ንዑድ መንፈስ የእኩልነት ማህደር ቢሆንልን። „እግዚአብሄር ለሰው ልጆች ይደክሙበት  ዘንድ የሰጣቸውን ጥረት አይቻለሁ።“ መጽሐፈ መክብብ ፫ ቁጥር ፲ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 18.02.2019 ከእመ ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። ጥሞና መልካምነቱ ብዙ ነገርን ከውስጥ ለማዬት ይረዳል። ሳተናው ድህረ ገጽ ስገባ የማነባቸው፤ ዩቱብ ስከፍት የማደምጣቸው ነገሮች መከፋቴን አሳየሉበት። ስለምን ብትሉኝ በ2008 ላይ የነበረው ድቅድቅ ጨለማ እና „ሰከን በል“ የአርቲስት ይሁኔ በላይ የህሊና ተቋም እኔን ያልተለመዱ እርምጃዎች ያስወሰዱኝ የጭንቅ ወቅት ነበሩና። እነዛ ያልተለመዱ እርምጃዎቼ ጥቋቁር ሰለነበሩ ያን መልክ ለማሳያዝ ደግሞ የግድ ጠ/ሚር አብይ አህመድ ወደ እጩ ጠ/ሚር ሲመጡ ማቃናት ነበረብኝ። እናም በድፍረት ያን ቁስለቴን የሚሸር ቀን ፊት ለፊት ዋዜማ ላይ ነው ብዬ የቀደመውን የጭንቀት መንፈስ የሚረገብ ጹሑፍ ጻፍኩኝ እና ለኩኝ። ኢህአዴግ ውስጥ የነበረው የለወጥ አዬር በጤናዳምነት በቅንነት ነው የተመለከትኩትና። ያተስፋዬ በ ኢህዴግ ውስጥ ከተሳካ ያን የመሰለ ምሬት ከእንግዲህ ለመላክ አላማሰቤን ስስበው እራሱ ጤናዬን መለሰለኝ። የዛሬውም የቀድሞዎችም ኢህአዴግ ላይ የነበረው ጠባሳ መሻሪያው የተስፋ ዘመን መጣ በሚል በትልቁ ሰፋ አድርጌ መንፈሴን እርጋ አልኩት። በዛ የውስጥ ቁስለት ውስጥ የታደሙ መንፈሶች እንደ እኔው ተስፋ ያደርጉ ዘንድ ደግሜ መማጸን ስለነበረብኝ ነው የማቃኛ ሌላ ደብዳቤ የጻፍኩት ለሚያደምጡኝ። አሁን የምሰማው የማዬው የማዳምጠው ደግሞ ለዬት እያለብኝ ነው። ዛሬ ጥዋት ከቀደመት አንጋፋ ጋዜጠኞች ውስጥ አቶ ኆኀተብ

አይዋ ምንትሶ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  አይዋ ምንትሶ። „በክፉዎች ምክር ያልሄደ በሃጢያተኞች መንገድ ያልቆመ እሱ የተመሰገነ ነው። በእግዚአብሄር ህግ ደስ ይለዋል።“ መዝሙረ ዳዊት ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie  18.02.2019                                     ይህ ለከብት ህልውና ብቻ ነው። እንዴት ናችሁ ውዶቼ? ደህና ናችሁ ወይ? ከዚህም ከዚያም፤ ከዚያም ከዚህም፤ እንዲህ ወደ ማዶ፤ እንዲያ ወደዛም ወደ ፈረፈሩ ... ቅይጥ ቅብጥር ምንት ሶ ነት ይደመጣል። ምኑ ተጨውቶ? በዚህም በዛም ቢመጣ። በዚህም በዛም ቢባዛም ጽናት በሌለው ዓላማ ዘመን ሰጥ ገጠመኞችን ዳክሮ ማዳከር አይዋ ምንትሶ ዛሬም እንደትናቱ እያስተናገደ ነው። በየሉም የሌሉዮሽ አዲስ ጠናና ቅብጥርሶ፤ ብልዝ ብርዳብርድ ባለው ሞ ግ ድ ባልተሰራለት ትናጋ ቢሉት ያም መብት ነው። ይቻላል እንደማለት። መብት ሲሆን ታዲያ በዬለም በተከዘነው አምክንዮ ውስጥ እንደ ቀደመው በማባጨል መሆን አይገባውም ነው ቁምነገር። ቅድሚያ አንድ ሁሉት ነገር ይዞ ብቅ ከማለት እራስ በዛ አመክንዮ ውስጥ ስለመኖሩ ፈተሽ ማድረጉ የተገባ ነው። ታዛቢዎች ስላለን። ያው የምንትሶ ነገር ሲረታ ደግሞ በምናምንቴው እሰኪጋፍን ድረስ … አይዋ ምንትሶ አዚማም ነው። መቀመም ያውቅበታል። ቀምሞ ድብን ያደርጋል። የዋዛ ለሴራ ማን ብሎት ተፈጥሮበት የለም።     ለነገሩ አድጦ አድጦ አንደላልጦ አንደላልጦ አሁን መለመላ ሲቀር ያው በፈረደበት ፍርደኛ ወደ አይዋ የኔታ የዋህዮት ተዝካሬን አውጣልኝ በሏል። ሲፍከረክ እንደለመደበት ማጣፊያው ሲያጥረው ጥግ ሁነኝ የሙጥኝ መባል የተለመደ ነው።  አይዋ ምንትሶ ትናንትም ምንትሶ ዛሬም ምንትሶ ነገም ምንትሶ

ሀውልት ለኑክሩማ ወይስ ለሥላሴ? ከጸሐፊ አቶ መስፍን ማሞ።

ምስል
 እንኳን   ደህና   መጡልኝ።  ሀውልት ለኑክሩማ ወይስ ለሥላሴ? “ለሁሉ ዘመን አለው፤ ከሰማይ በታችም ለሆነው ነገር ሁሉ ጊዜ አለው።” መጽሐፈ መክብብ ምዕራፍ ፫ ከቁጥር ፩ እስከ ፪ መስፍን ማሞ ተሰማ ሠላም ለናንተ ይሁን! {ማስታወሻ፤ ውድ አንባቢ! ቀጣዩ ፅሁፍ የተነቀሰው <ሞትና የኢትዮጵያ መሪዎች> በሚል ርዕስ በ381 ገጾች ህዳር 2006 ዓ/ም - 2013 - በአነስተኛ ቁጥር በሲድኒ ካሳተምኩት መፅሀፍ ነው። በዚህ መፅሀፍ የግርማዊነታቸውን ዘመን በሚተነትነው ምዕራፍ ዛሬ በሰፊው መነጋገሪያ የሆነው <የኢትዮጵያ ፓን አፍሪካውያን> በሚል የተደራጀው ማፍያ የህወሃት መንግሥታዊ ቡድን የግርማዊነታቸው ሀውልት በአፍሪካ ህብረት ግቢ እንዳይቆም በታሪክና በትውልድ ላይ የሰራው ሸፍጥ በዝርዝር ቀርቧል። ከአምስት ዓመት በፊት በታተመው መፅሀፍ የሚከተለው ትንተና ቀርቦ ነበር፤ መልካም ንባብ ይሁንልዎ!}        አቶ መለስና መንግሥታቸው ቀዳማዊ ሃይሥላሴ ለአፍሪካ ያበረከቱት አስተዋፅዖ እንዳይዘከርም ሆነ ቋሚ ሀውልት እንዳይተከልላቸው በፅኑ የጣሩና ጥረታቸውም ፍሬያማ እንዲሆን ያደረጉ ናቸው።  “የኢትዮጵያ እንቆቅልሽ፤ ሀውልት ለኑክሩማ ወይስ ለስላሴ?” Ethiopia’s conundrum: A statue for Nkrumah or Selassie?  በሚል ርዕስ የአፍሪካ ሪፖርተር ጃኔት ሾኮ / Janet Shoko/ ፌብሩዋሪ 8፤ 2012  ካቀረበችው ዘገባ የሚከተለውን ልብ ይሏል፤  የቀድሞውን የጋና መሪ ኳሚ ኑክሩማን ለመዘከር ሐውልታቸው በአፍሪካ አዳራሽ መተከሉ አግባብ ነው ሲሉ አቶ መለስ ጥብቅና ቆመውላቸዋል። የሃይለ ሥላሴ ሐውልት እንዳይተከልም ዐይነተኛ መከራከሪያቸው ያደረጉት፤ ኑክሩማ ፓን

የማረተው የደራጎን ዝልቦ አይዋ ጎርምድ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  የማረተው የ ደራጎን ዝልቦ። “ … ስለዚህ ክፉዎች፤ በፍርድ፤ ኃጢያተኞችም በፃድቃን ማህበር አይቆሙም፤ እግዚአብሄር የጻድቃንን መንገድ ያውቃልና። የክፉዎች መንገድ ግን ትጠፋለች። መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፩ ቁጥር ከ፭ እስከ ፮ ከሥርጉተ © ሥላሴ Sergute © Selassie 16.02.2019                                   ይህ የሆነው ለላንቲካ አይደለም! ·        መነ ሻ http://www.zehabesha.com/amharic/archives/94071#comments “ ጎንደር የራሱን ክልል መመስረት አለበት ” – የጎንደር ሕብረት ፕሬዚዳንት ዶ / ር ሙሉጌታ ካሳሁን እም! እማይሰማ የለም? እነ የሙት መሬት ባልደረባዎች እነ አያልቅበት ሌላ የሰላ ባለሦስት ጥንዙል የጨለማ ማቃዊ - ድቅድቅ - ሙርቅርቅ ዜማ ደግሞ ይዘው ከች ብለዋል። እነ የጎንደር ህብረት። ለጎንደር ህብረት ዛሬ ሥም ላወጣለት ፈለግሁኝ። ጎርምጥ ብዬ።  ውዶቼ ደህና ዋላችሁልኝ። ደህና ናችሁ ወይ? ናፍቆት በናፍቆት በብራና ፍቅርም ይላክላችሁ የእውነት ንፍቅ ብላችሁኝ ነበር የሰነበታችሁት። እኔ ግልጽ እና ቀጥተኛ ሴት ነኝ። የምላችሁ የሆንኩትን ነው። የጎንደር ህብረት መርዝ አላባራ አለሳ?                                           ዕውነት ይህን ያውጃል! ዛሬ ነው ከሳተናው ስቀጥል ዘሃበሻ ላይ አንድ ገዳይ መንፈስ ደግሞ ያገኘሁት። ከሲኦሎች ማህበር የተቀመመ አዲስ ቅይጥ ትርትር፤ በትን የተባለለት፤ ሸንሽን የተባለለት የመንፈስ መርዝ ነው። ጎንደር ብቻውን ለማሰቀረት ያተሰበ የተለመ መሰሪ ደ