ልጥፎች

የአቶ ወንድም የ ጋዜጠኛ ፋሲል የኔአለም ተረብ...

ምስል
የጋዜጠኛ ፋሲል ተረብ ማለዘቤያ ቁራሽ መላሾ ነው። „አቤቱ በድንኳንህ ውስጥ ማን ያድራል ?“ መዝሙር ፲፬ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ  21.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። እንዴት ናችሁ የኔዎቹ። ደህና ናችሁ ወይ? ትናንት ዳውን ሎድ ማድረግ ተቸግሬ ጹሑፌን ሳላወጣ ቀረሁኝ። የትናንቱ በሌላ ዙሪያ ነበር። ዛሬ እሺ ካለ ይሞከራል። ስለዚህም ትናንት ቀጥዬ ልጽፍ የነበረኝ ፍላጎት ከፈጣሪ ፈቃድ ጋር ነው ብዬ በሌሎች የንባብ ፕሮግራሞች ላይ አተኮርኩኝ። ዛሬ በአዲስ አጀንዳ ብቅ አልኩኝ። https://www.zehabesha.com/amharic/archives/92059 የአዴፓ መሪዎች ምን ይላሉ ? – ፋሲል የኔዓለም እንድምን አለህ ወንድም አለም ልጅ ፋሲል የኔአለም። ደህና ነህ ወይ? ውዶቼ፣---- ዛሬ ከአቶ ወንድም ከጋዜጠኛ ፋሲል የእኔ ዓለም ጉዳይ ጋር አብረን እንዘናከት ዘንድ ወደድኩኝ። ጥሩ ነገሩ እንደ ድርጅቱ እንደ ግንቦት 7 አይደለም እሱ። ወቃሰው ሆነ ሙግቱ ቂም አብቅሎ ዘመቻ ግለት ጫና የሚያስከትል አይደለም። እንዲያውም እኔ እስኪ በቃው ሞግቼው ወጣቶች እንደ ነገሩኝ ከሆነ አንድ ጹሑፌን በቤተ መንግሥቱ ሚዲያ በአምስተርዳሙ ኢሳት እንደ አቀረበው ነግረውኛል። እስኪ ገርመኝ ድረስ። በሌላ በኩል አንድ ጊዜም አንድ ሃሳብ ኖሮኝ ስጽፍለት በጎ መልስ አክብሮ ሰጥቶኛል። ይህን በራሴ ደርሶ ስላዬሁት በአንድ ወቅት በዝርዝር ጽፌያለሁኝ። ሌላው ትልቁ ጸጋው የፈለገ አስተያየት ይጻፍ አክብሮ መልስ ይሰጣል። ትህትናው እንዲያውም እናቴን እብዬን ይመስለኛል። እናቴ የባዛ እጅግም የበዛ ደግ ቅን እና ትሁት ናት። ትህትናዋ ስለሚበዛ ልጆቿኝ እንደ ትዳሯ ታከብራለች፤ ትፈራናለችም። አዘዦቿ እኛ እንጂ እሷ አይደ

የሥልጣኔ ድንጋጌ ጥሩ ዜና በበተልሄም ብሥራት ሲሰክን!

ምስል
የማግስት ብሥራት ድንጋጌ ናት የፈጠራ ባለቤቷ ወጣት ቤተልሄም ደሴ። „ሁሉም በመቅደሱ ምስጋና ይላል።“  መዝሙር ፳፰ ቁጥር ፱ ከሥርጉተ©ሥላሴ 19.10.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ።፡ ማስተዋሏ የበረከተ ነው። ቅኝቷ ለምለማዊ ነው። እረቀቷ እዬራዊ ነው። በዓላማው ውስጥ ከዕድሜዋ በላይ የሚጠይቀውን ትዕግስት ተጎናጽፋ በአማኑኤል ተሰጥቷትም ሐሤትን በተሟላ ተስፋ በገፍ አጋርታናለች። ብርክታዊት! ለኢትዮጵያ አገሬ ሽልማትም ናት። እሷም ደስተኛ ናት። እውነት በማይመስሉ የኮንፒተር ሳይንስ ፍልስፍናዎች እና ውጤቶች ተሰማርታ ስኬታማ ሆናለች። ዕድሜዋን ሳያስቡ ተግባሯን ብቻ ማሰቡ ብቻ ይሻላል። ዕድሜዋን አስበው የህይወት ጊዜዋን ሲያስተውሉ ልበወለድ ስለሚመስል። „ለእግዚአንሄር ግን የሚሳነው የለም“ ማለቱ ለአማንያን ታምራቱን ያይ ዘንድ የሆነው ሁሉ እንዲህም ሆነው። ብሩሕ ቢዥነር ናት። እማጅነሽኗ እርቀቱ ይገርማል። የምትገርም ዕንቡጥ ቀንበጥ ፈላስፋ ወጣት ናት። ለ21ኛው ምዕት የተፈቀደላት ባለመክሊት ናት። እውነትም ቤተልሄም የዬምስራች ዓውደ ምህረት የሥልጣኔም ጥሩ ዜና።   የሚገርመው በዚህ ዕድሜዋ ልዑል እግዚአብሄር እኛን የሰጠበት ሚስጥር ደርሳበታለች። አትጨናነቅም፤ መጨናናቅንም አጀንዳዋ አለደረገችውም። ብሩሁን ጭንቅላቷን ማበከን አትፈቅድም እና። ጊዜዋን ባልባሌ ጉዳያዎች አታሳልፈም። ጌዜ ወርቅ ነው ገቢር ላይ ውሏል። ደስታ ተስጥዖችን ስለመሆኑ እዬኖረችበት ነው። ህይወትን ቀለል ዘና አድርጎ መኖርንም በዚህ ዕድሜዋ ታስተምረናለች። ፍልቅልቅ ያለች፤ ቀለል ያለች ቁጥብ ወጣት ብርሃን ጠገብ ወጣት ናት። የተስፋ ውሃ ልክ ንጥረ ነገር እርጋታዋ የችግር መፍቻ በእጇ ስላለ ብቻ ሳይሆን ኢማጅኔሽኗ