ልጥፎች

ተፈጥሯዊ አቀባበል።

ምስል
      ተፈጥሯዊ             አቀባበል። „አንተ ፊቴን እሹት ባልክ ጊዜ  አቤቱ ፊትህን እሻለሁ፤ ልቤ አንተን አለ።“  መዝሙር ፳፮ ቁጥር ፰ ከሥርጉተ © ሥላሴ  ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ 08.11.2018 ·     መነሻዬ። https://www.youtube.com/watch?v=N01J5vKDPbQ Ethiopia: የፈረንሳይ ወጣቶች “ ንግስታቸዉን ” ብርቱካን ሚደቅሳ በደመቀ ሁኔታ ተቀብለዋታል !! ዛሬ ክብርት ዳኝ ብርቱካን ሜዲቅሳ ኢትዮጵያ ገብታለች። የመንግሥት አቀባልን ፎተውን አይቸዋለሁኝ። እኔ የመሰጠኝ ግን የወጣቶቹ ልዩ የቀይ ምንጣፍ አቀባበል ስለሆነ ትንሽ ልልት ወደደኩኝ። ባጋጣሚው አንዳፍታንም ላመስግን ለቅንብሩ ጥራት ሙሉውን ተከታትዬዋለሁኝ። ክብርት ዳኛ ብርቱካን ሚደቅሳ ውስጧን አቅሟን ጥረቷን በቅንነት ለማበርከት አገር እንደገባች አምናለሁኝ። እያንዳንዱ እንቅስቃሴዋ የጥጋናዊ ለወጡን በመደገፍ፤ በማገዝ፤ በማበረታት ጥንካሬ በመስጠት ላይ እንደምትተጋም አስባለሁኝ አምናለሁኝ።  ለረጅም ጊዜ በአካል እንዲህ ልናያት ባለመፈቅዷ ብከፋባትም ዛሬ ሳያት ግን ሰውነቷም መንፈሷም ሙሉ መሆኑን ለመመልከት ችያለሁኝ። የሆነ ሆኖ ዛሬ በነበረው የጀግኖቹ የፈንሳይ ለጋሲዮን ኢትዮጵያዊ አንበሶች የአቀባባል ዝግጅት ላይ ቁምነገሩ ተፈጠሯዊ መሆኑ ነው ቀልቤን ስቦት ብዕሬን እንዳነሳ ያደረገኝ።  በነገራችን ላይ በድምጽ እማውቃቸውን ወላጅ እናቷን መኪና ውስጥ ወ/ሮ አልማዝን በጨረፍታ ለማዬት በመቻሌ እንኳን ለዚህ አበቃቸው ማለትን እሻለሁኝ። የኢትዮጵያ እናቶች እንዲህ ዓይነት ልጅ ሲወልዱ ፈተናውም የእነሱ ነውና። እሷንም እንኳን ለአገርሽ መሬት በሰላም አበቃሽ ማለትን እፈቅዳለ

ኃላፊነት የሁሉም ኃላፊነት ነው።

ምስል
ኃላፊነት የሁሉም ኃላፊነት ነው። "የአምላክ ልጆች ሆይ ለእግዚአብሄር አምጡ፤ ክብርና ምስጋናን ለ እግዚአብሄር አምጡ።" መዝሙር ፳፰ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ  08.11.2018  ከጭምቷ ሲወዘርላንድ። ጤና ይስጥልኝ የኔዎቹ እንዴት ናችሁ? ደህና ናችሁ ወይ? አቅምን፤ ብልህነትን፤ ታማኝነትን፤ መልካም ነገርን ማዋጣት ማግስትን ያሳምራል። ባለፈው ዓመት ይህ የጥገናዊ ለውጥ አዬር መደገፍ አስፈለጊነት አስመልክቶ ብዙ ነገሮችን ብያለሁኝ። መልካሞቹ ሰዎች ጥረትን አህዱ ሲሉ የተጋሁበት ምክንያት ሁሉም የአቅሙን ማድረግ ከቻለ ዛሬን ማግኘት ስለሚቻል፤ ዛሬን ማግኘት ከተቻለ ነገ እና ከዚያም ወዲያን ማግኘት ስለሚቻል ነበር። እኔ ዛሬ ማንሳት የፈልግኩት ስለ ኃላፊነት ጽንሰ ሃሳብ ትንተና ልሰጥ አይደለም። ግን ነገር ግን ኃላፊነትን ወደ ሌላ ከማሻገር በፊት እራስ ላይ ያለውን ኃላፊነት በቅድሚያ መወጣት ይገባል ለማለት ነው። ሁሉንም ነገር መንግሥት ሊከውን አይችልም። በሰለጠነው አገርም ብዙውን ሃላፊነት የሚሸከመው ህዝብ፤ የሃይማኖት ተቋማት እና የሲቢክስ ድርጅቶች ናቸው። ኢትዮጵያ ላይ ለዛውም የ50 ዓመት ቁልል ችግር አልበቃ ብሎ በተደራጁ ሃይሎችም የተሰሩ ሰው ሰራሽ ችግሮችም አሉበት። የሆነ ሆኖ ችግርን በማውራት ችግር አይቃለልም። የሰው ልጅ የአኔ ኃላፊነት ይህ ነው ብሎ መቀበል መቻል አለበት። ግዴታን እዬተወጡ መብትን መጠዬቅ ልንከተለው የሚጋባ መርህም ነው። ጥገናዊ ለወጡን መተቸት እችላለሁ ግዴታዬን ግን አልወጣም ማለት ሥርዓለበኝት ነው። ካለ ግዴታ መብት ካለመብት ግዴታ ኑረውም አያውቁም።  ለምሳሌ ልጆችን በሞራላዊ ዕሴት ማነጽ የወላጆች ንጥር ግዴታ ነው። ልጆች የሰውን ልጅ እንዲያከብሩ፤ እንዲያፈቅሩ፤ እ

ጎንደር እንግዳዋን ፕ/ ኢሳያስ አፈወርቂን ነገ እልል ብላ መቀበል ይኖርባታል።

ምስል
ጎንደር እና ነገ። „አግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ።“ መዝሙረ ዳዊት ፳፮ ቁጥር ፲፬ ከሥርጉተ©ሥካሴ  08.11.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ ነገ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጎንደርን እንደሚጎበኙ እዬተነገረ ነው። እኔ ያልወደድኩት የአማራ እና የኤርትራን የብቻ ለብቻ ግንኙነት እንጂ ማዕካላዊ መንግሥት በሚመራው ከሆነ መልካም ነገር ነው። ጠ/ሚር አብይ አህመድም አብረው እንዲመገኙ አዳምጫለሁኝ። አንዲት ሉዑላዊት አገር ከጎረቤት አገሮች ጋር የሚኖራት ግንኙነት በዚህ መልኩ ነው መከወን ያለበት። በስተቀር ሥርዓተ አልበኝነት እና ፍንገጣ ይመጣል። መርሁም አይፈቅድም። ቤተሰባዊ ትውፊቱ ሆነ ትሩፋቱ ግን ያው እንደ ተጠበቀ ሆነ። ምናችን ይለይ ነበር። DNN የሁለታችንም አንድ ዓይነት እኮ ነው። መለዬት አያችልም።   በነገው ጉብኝት ላይ የወልቃይት እና የጠገዴ ሆነ የራያ እና የመተከል ጥያቄዎችን መፈክር ይዞ መውጣት በፍጹም የተገባ አይደለም። እንግዳ ለማስተናገድ እንደ አባት አደሩ የበሞቴ አፈር ስሆን ጉርሻ የፍቅር እንጂ ሌላ መሆን አይኖርበትም። የተገባው የህዝቡ ጥያቄ ባለፈው ጊዜ ወጥ በሆኑ ሁኔታ ከ10 ባለነሱ የአማራ ክልሎች ቀርቧል። ከዚህ በላይም በተለያዬ ሁኔታ በግልም በጋራም አቅርበናል። አሁን እንግዳ ነው የሚመጣው። እንግዳ በአባባ በጉዝጓዝ፤ በመና ዳቦ፤ በሳቅ፤ በፈገግታ በደስታ ነው አቀባበል መሆን ያለበት። ቀደም ብዬ በተከታታይ እንደ ተናገርኩት የኤርትራ እና የኢትዮጵያ ሰላም መሆን ከማንም በላይ ለጎንደር ነው ተጠቀሚ የሚያደርገው። ምክንያቱም ከፋኝ ያለው ሁሉ መሸጋገሪያው ጎንደር ነው። ምሽጉ ደግሞ ኤርትራ ነው። ኤርትራን ማግኜት ያልቻለ ሁሉ ቁንጫኑን የሚወጣው በጎንደር ላይ ነው። በዚህም የጎንደር እናት ዓመት

ጎንደር አደብ መግዛት አለበት። ሰላሙንም መጠበቅ ግዴታው ነው።

ምስል
ጎንደር ልብ ይግዛ!አደብም ይኑረው! „ሃሌ ሉያ።  እግዚአብሄርን በመቅደሱ አመስግኑት።“  በሃይሉ ጠፈር አመስግኑት።“ ከሥርጉተ©ሥላሴ  07.11.2017 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ                                               https://www.youtube.com/watch?v=q2vm1rTRJgY ከንቲባ ዶክተር ሙሉቀን ስለተበተነው የውሸት ወረቀትና እና ስለሰሞኑ ጉዳይ የተናገሩት 28,02,2011 አሁን ከሆነ ኤቢ አድበርታይዘመንት የሚያዘጋጃቸውን ቅንብሮች እከታተለሁኝ። ተመስገን ብያለሁኝ። ነገረ ጎንደር ነገረ ሥራው መከረኛ ስለሆነ መረጃዎች ጭጭ ሲሉ ይጨንቀኛልና። በመንግሥት ደረጃም ከሚዲያም የተገለለ ነው ጎንደር። ጎንደር የሚፈለገው ኧረ ጎራው ሲፈልግ ብቻ ነው። አሁንም ጫና በጠ/ሚር አብይ አህመድ ላይ እንዲኖር ስለሚፈለግ ሲጯጯኽ አዳምጣለሁኝ።  የአብይ ለማ መንፈስም ለጎንደር ቀልቡን መስጠት ይኖርበታል። አሁን የተመረጡት ከንቲባ ዶር ሙሉቀን አዳነ ልክ የሱማሌው ችግር በተፈታበት መንገድ አይነት ነው። የዚያን ያህል መንፈስ በገፍ ሊሰጠው ይገባል። ብአዴንም ዕድለኛ ነው እንዲህ አይነት ብረት መዝጊያ ሊሂቅ ጎንደር ላይ ማግኘቱ።  የጎንደር ከተማ ከንቲባ ዶክተር ሙሉቀን አደና በተለያዩ ወቅቶች ያደረጉትን ቃለ ምልልስ እና ንግግር አዳምጫለሁኝ። ለሁሉም እኩል አገልግሎት ሊሰጡ የሚችሉ ቅን ሰው መሆናቸውን ከንግግራቸው መረዳት ችያለሁኝ። የጎንደር መዘጋጃ ቤት ለዘመናት መጋጃ ቤት ሲባል ነው የኖረው። አሁን እንደ ዕድል ሆኖ እንደዚህ ንግግራቸው እና ልሳናቸው ሊደመጡ የሚናፈቁ ከንቲባ መገኘታቸው እኔን እራሱ ገርሞኛል። ተዬት ተገኙ ሁሉ ብያለሁኝ። የሥ

"አግዚአብሄርን አመስግኑ።"

ምስል
„አግዚአብሄርን አመስግኑ።“ „እግዚአብሄርን አመስግኑ መዝሙር መልካም ነውና።  ለአምላካችን ምስጋና ያማራ ነውና።“ መዝሙር ፻፵፮ ቁጥር ከ፩ እስከ ፪ ከሥርጉተ©ሥላሴ  07.11.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዝሻ "በስም አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አህዱ አምላክ። አሜን!" ውዶቼ እንዴት ናችሁ ዛሬ ደግሞ ተነስቶብኛል። እቸከችከዋለሁኝ። ·       እ ንዲህም ሆነላችሁ … አዲስ ብርሃናማ የምሥራች ሰንበት ላይ አዳመጥኩኝ። ሰንበትንም በሰላም አሳለፍኩኝ ሻማዬን ቦግ አድርጌ። ምክንያቱም ዕለታዊ ዜና መስማት የምፈልግበት አንድ አውደ ምህረት ስላለ። ያም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አህታዊነት ቀጣይነት ጉዳይ ነው። ሃይማኖታዊ ጉዳይ ከነባቢት በላይ ነው። ብዙ ሰው ተቋም የለውም ጥገናዊ ለወጡ ሲል አዳምጣለሁኝ። በመንፈሳዊ ህይወት የሁለቱም ሃይማኖቶች የእስልምና እና የቅድስት ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ሃይማኖት ለማስማማት አንድ ለማድረግ የተወሰደው እርምጃ እና የተከወነው ተግባር ለመንፈሳዊ ህይወት ታላቅ ተቋማዊ ውጤት ነው። አላዛሯ ኢትዮጵያ እግዚአብሄር / አላህ አላ ብላ ስለምታምን ተከታዮችም እልፍ ስለሆኑ በዚህ ዘርፍ የተከወነው ዕሴታዊ ትውፊታዊ ተግባር የቆሰለውን ታሪካችን ደግሞ የፈጠረ ነው ማለት ይቻላል ። ሁለት ትልልቅ ባላዎች አሉት ጥገናዊ ለውጡ። ጸሎቱም ነው በተከታታይ ከሞት ከተቃጣ መከራ ጠ/ሚር አብይ አህመድን በዬጊዜው እዬታደጋቸው ያለው። ጸሎት /ደዋው ከተወረወረ ሰይፍ ይታደጋል። የቅድስት ኦርቶዶከስ ብጹዕን አባቶች በዬሚገኙበት ውጭ አገር አይናችሁ ጥርሳችሁ ከሚባሉበት እንክብካቤ እና ቁልምጥ ወጥተው ወደ አገር እንገባለን ብለው ሲወስኑ ከአንድነት በላይ ምንም ስሌለ ብንፈልገውም ከ