ልጥፎች

የኢዴፓ እጩነት /አዲስነት ትልሞሽ/

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  የኢዴፓ እጩነት። የሚቀድመው   የትኛው ይሆን? ግን ገነገነ   ወይንስ ገነነ ልበል ከቶ! „የፃድቃን አፍ ጥበብን ያስተምራል፤ አንደበቱ ፍርድን ይናገራል።“ መዝሙር ምዕራፍ ፴፭ ቊጥር ፴ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 25.02.2018 ከእመ ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። ትናንት በዋለው የአጋር ድርጅቶች ይሁን የአጋር ክልሎች ዓወደ ህዝባዊ ስብሰባ ጠ/ሚር አብይ አህመድ ወደ ወጥ ፓርቲነት ድርጅታቸው እንደሚሸጋገር አብስረዋል። ጉደኛው ኢህአዴግ ወደ „ኢትዮጵያዊ ፓርቲነት“ ሊለወጥ ደስ ይላል። ኢትዮጵያዊ ፓርቲነቱን ሲያልም ግን የቋንቋ ፌድራሊዝምን ተሸክም ይሆን?   ብቻ መሰናክሉን ማለፍ ከተቻለ ወሸኔ ነው ማለፊያ። መሰናክሉ የህሊና ለውጥን ነው የሚጠይቀው። የቅርቡን የወ/ሮ ሀቢባ ሲራጅ ቃለ ምልልስ ብቻ በቂ ነው። ምን ያህል የዘለበ ገማና ኢትዮጵያ እንዳለባት። አሁን እንኳን በዬቦታው የራስን ሰው ለመሸጎጥ ማራቶኑ ተንጠራርቶ አገር እያመሰ ስጋት እያቀና መሆኑ ነው የሚደመጠው። የሳቸው ቸር ምኞት ግን ሁልጊዜም ይገርመኛል። እስኪ ያሳካላቸው … አሜን አሜን ይሁን ይሁን ብለናል።      ወደ ቀደመው ምልሰት ሳደርግ እኔ እንዲያውም ኦዴፓ አውራ ፓርቲ ሆኖ ለመውጣት ሥም ሲያድል ብአዴን ተቀብሎ አዴፓ ነኝ ከዛሬ ጀምሮ ሲል ምን አለ ኢዴፓ ብትባል ብዬም ነበር/ የኢትዮጵያ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ። / ማለቴ አማራ ክልል ነው እና ኢትዮጵያዊነትን ተሸከም የሚበላው በዬዘመኑ። እነ አቶ በረከት ስምዖን፤ እነ አቶ አዲሱ ለገሰ፤ እና አቶ ዮሴፍ ህላዊ፤ እነ አቶ ተፈራ ዋልዋ፤ እና አቶ አለምነህ መኮነን ምን ተዘርዝሮ ሲያልቅ ... አሁንም ስልጣን ምንችንም አይደለም

የኢትዮጵያ ህዝብ መኖርን ነው በትህትና እዬለመነ ያለው።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ርህርህና የመሰረት ድንጋይ። „በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ“  መዝሙር ፴፰ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 25.02.2018 ከእመ ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። ይህ ኪዳን የሁልጊዜ እንዲሆን እመኛለሁኝ! ጤና ይስጥልኝ ውዶቼ እንዴት ናችሁ? ደህና ናችሁ ወይ? ኦህዴድ እውን ኦዴፓ ከሆነ ልለው የምሻው ነገር ይኖረኛል ዛሬ። ከሁሉ በፊት፤ ከሁሉ አስቀድሞ መከወን ያለበት መሪዎቹን በዬደራጀው ያሉትን በፌድራልም ይሁን በክልሉ ሆነ በዞን ይሁን በወረዳ የሚያስቀምጣቸውን ወገኖች ሞራላዊ ሰብዕን መገንባት ያለበት ይመስለኛል። አውራ ፓርቲ ስለሆነ አብነቱ ከዛ ነው የሚጀምረው እና። ሁለቱም በፍጹም የተገራ ሰብዕናቸው ነው ህዝብ ከሰማይ እንደወረዱ መላዕክት የሚያቸው። እና ተከታዮቻቸውም እንደ እነሱ እንዲሆኑ ማድረግ ግድ ይላል። ከሁሉ አሰቀድሞ ከሁሉም በፊት የህዝብ ሃላፊነት ለመስጠት ከማቀዱ በፊት ሁሎችም በውስጣቸው የቋጠሩትን ቂም በቀል እና ቁርሾ እንዲያራግፉት ማድረግ ይጠበቅበታል - ኦዴፓ። በሩን ዝግት አድርጎ፤ ከሚዲያ ውጭ በሆነ ሁኔታ ይምከር - ኦዴፓ። በውነቱ እጅግ የሚያሳዝኑ ነገሮች ነው የሚታዩት። የሚደመጡት። የእኔ ለመባል የእኛ ማለትን ይጠይቃል። አብሶ እላፊ መሄዱ ነው የሚጎረብጠው ከሚፈጸው አሰቃቂ ኢ-ሰብእዊ ተግባር በላይ።   በአዲስ አባባ ጭፍጫፋ እና እስር ጉዳይ "ዘራፊ፤ ሃሺሸኛ፤ ሌባ ወሮበላ" ነበር የተባሉት የተሰዉትም የታሠሩትም ዜጎች። አሁን ደግሞ "ህገ ወጥ ወራሪዎች ናቸው" የሚባሉት በለገጣፎ ያሉ ነዋሪዎች ዜጎች። ትናንትም የነበረው እራሱ ኦህዴድ ነው፤ ዛሬም ያለው ኦህዴድ ነው ራ

ይባረኩ! ጸሐፊ አቶ ግርማ ካሳ።

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ይባረኩ  ጸሐፊ አቶ ግርማ ካሳ። „በጎ ነገር ማድረግ ሲቻልህ፤ በወዳጆችህ ላይ ክፉ አትስራ።“ መጽሐፈ ምሳሌ ፫ ቁጥር ፳፰ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 24.02.2019 ከእመ ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። ·          መነሻ። https://www.satenaw.com/amharic/archives/64150 የአቶ ንጉሱ የተለሳለሰ አስተያየት ግፈኞችና ዘረኞችን የሚያበረታታ ነው ( ግርማ ካሳ )   February 24, 2019 የኔዎቹ እንዴት ናችሁ? ዘለግ ላለ ጊዜ በአቶ ንጉሡ ጥላሁን ላይ ሰፊ ማብራሪያ ስጽፍ ቆይቻለሁኝ። መጀመሪያ ጠ/ሚር አብይ አህመድ  ወደ ስልጣን እንደመጡ የልብ ስለሆኑ ለኦህዴድ ቃለ ምልልስ OBN አድርገው ነበር። አንዲትም ቦታ „ኢትዮጵያ“ ሲሉ አላዳምጥኳቸው። „በአገሪቱ ተጀምሮ በአገሪቱ ተጠናቀቀ“ እራሱ ቃለ ምልልሱ ደመመን የተጫነው ነበር። አንዳች ምናምን በተጫነው መንፈስ ውስጥ በጭንቅ የሚወጣ ቃል ነበር ያዳመጥኩት። ከዚህ ጊዜ በሆዋላ እሳቸውን መከታተል ጀመርኩኝ።  በጠ/ሚሩ በመጀመሪያ ጉብኝትም ወደ አማራ ክልል ባደረጉበት ጊዜ የታዘብኩትን ታዘብኩኝ። ለውጡን በመቀበል አይደለም ችግራቸው እኔ እንደማስበው። ዶር ለማ መገርሳ ጠ/ሚር ቢሆኑ እንዲህ ፈተና አይሆኑም ነበር። ውስጣቸው ቁርሾ አለበት። እኔስ እንዴት አንሳለሁ የማለት።  በለውጡ ውስጥ ገነው የወጡ ሥሞች ረብሸዋቸዋል ብዬ አስባለሁኝ። ከሁሉም የከፋው ግን በሚሊዬነም አዳራሽ ለአባገዳ ጃዋር መሃመድ ያደረጉት ቅጥ ያልተሠራለት የፈጠጠ ገመና ነበር። ያ በውነቱ ክብደታቸውን በ እጅጉ ቀንሶታል። ከኢትዮጵያዊነት በላይ ክብር የለም። ኢትዮጵያ