ልጥፎች

ሁለተኛው ምዕራፍ የኳስ ዊድንግ ሻውር ... በመስኮ።

ምስል
124 ደቂቃ በመስኮ „በችሎቱ አምስግኑት በታላቅነቱ አመስግኑት።“  (መዝሙረ ዳዊት ምዕራፍ ፻፶ ቊጥር ፪) ከሥርጉተ ሥላሴ 11.07.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ) 90 ደቂቃ አልበቃኝም አለች። ናፈቀችው የኮራን ድልቃ እናም እሲከ በቃት ድረስ ተደቃች፤ ተሰለቀ፤ች ታሸች፤ ተሸከረከረች፤ ዳናሰች እስክሰክታውንም አስነካቸው….   ሁለተኛ ምዕራፏን ዊድንግ ሻውሯን ከኮራ ጋር አሳምራ ከውና ኮከቤ ለኮራ አሰኝቶኛል ስትል ወሰናች እቴዋ ድንቡልቡሊት ለዋንጫ ከመረጠቸው ጋር ከፈንሳይ አገር ሰንበት እንገናኝ ብላለች። ኮራዝድንገቴ ናቸው። እንደ ሽምቅ ተዋጊ አደጋ መጣል ይችላሉ። የሰውነት አቋማቸው ጠንካራ ነው። እንዳልኩት ኮራ ለዋንጫ ውድድር ከፈራንሳይ ጋር ይጋጠማሉ ብዬም ነበር ትናነትና። ባለፈው ሳምንት መሸኛ ላይ የጨዋታ ጊዜ ተራዝሞ ያም አልሆን ብሎ በፔናሊቲ ነበር ኮራ ራሺያን በባዕቱ ስደት ልኮ ነው ለዛሬ ቀን የበቃው …. እንግሊዞች በጥዋቱ ቀንቷቸው ነበረ። ብዙ ጊዜ ነፃ ምት ክርስቴኖ ሮናልዱ ነበር ለግብ የሚበቃው፤ ዛሬ እንግሊዞችን ቀንቷቸው የመጀመሪያ ግባቸውን አገኙ። በጥዋቱ ነበር ደስታ እንኳን ደህና መጣችሁ ያላቸው። ኮራ ትንሽ ግፊያ አብዝተው ነበር የቆዩት በሰጨኝ ብለው። የሆነ ሆኖ 68ኛው ደቂቃ ላይ ቀናቸው እና ቀጥለው ተፋልመው 90ው ደቂቃ በእኩል ነጥብ ጨዋታው ተራዘም። ጎሏ አገባቧ የነፍስ ያህል ነበረች። ወርቅ ነበረች። መጨረሻ ከሁለተኛ እረፍት መልስ ኮራ አቅሙ አጣናክሮ በትጋት እና በተከታታይ የማጥቃት ጥበብ ጥረቱ ተሳክቶ 109 ዲቂቃ ላይ ለስኬት በቃ።  ስለሆነም እንግሊዝን 2 ለ 1 በመሸኝት ለዋንጫ ከፈርንሳይ ጋር   የመጨረሻው ጨዋታ ይኖረዋል። ጨዋታን ከአሸነፈ የመጀመሪያው ዋንጫ ነ

መሆን ይቅደም!

ምስል
ህልምህን ስታገኘው በህልምህ ውስጥ ለመኖር ፍቀድ። „አስተዋይ መልካም ምክርን ገንዘቡ ያደርጋል“ (ምሳሌ ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፭) ከሥርጉተ ሥላሴ 11.07.2018 (ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ) ·        ጠብታ። የሚገርሙኝ ነገሮች እጀግ በራካታ ናቸው ዛሬ ጥዋት ዩቱብ ያቀረብልኝ የዓለም አቀፍ ጋዜጠኛው የአቶ አለምነህ ዋሴ ዶር ለማ መgርሳ ለጨፌ ኦሮምያ ጉባኤ ያደረጉትን ንግግር መሰረት ያደረገ ነበር። „የያዙት ወርቅ ከመዳብ ቁጥር“ ነው እንዲሉ ያገኘነውን ወርቅ አያያዝ እንወቅበት የሚል ሁለንትና ዕድምታ አለው። እኔ ደግሞ የቀደመውን ብሂል ገልበጥ ላድርግ እና የያዙት ወርቅ ከመዳብ ሳይሆን ከብረትም አንሷል ባይ ነኝ። አዎን ዘመናይነቱ፤ ቅልጣኑ፤ የኬክ ቁረሱልኝ አቃቂሩ ስለሚያቅለሸልሸኝ። የትም ዓለም በዚህ በ100 ቀን ታይቶ የማያውቀውን ትንግርት ነው አላዛሯ ኢትዮጵያ እያስተናገደች ያለችው፤ ዕውን አላዛሯ ኢትዮጵያ ናት ይህን ሁሉ የተግባር ዕንቁ በመሰብሳብ ላይ ያላቸው ያሰኛል? እኔ የጠበቅኩት ነው። ከመጀመሪያውም ጀምሬ የተጋሁበት ነው። እንዲያውም ይህ በግራ በቀኝ ውጥረት እና የሰላም ህውከት እዬተዋከበ የተከወነ ሲሆን የተረጋጋ ሁኔታ ቢገጥመው ምን ሊሆን እንደሚችል ሳስበው እራሱ ደረጃም፤ ልክም ለማውጣት ይቸግረኛል። ህውከቱን የወያኔ ሃርነት ትግራይ በፊታውራሪነት ያልታደለ በሉትና፤ ሌሎቹ ደግሞ የቤተመንግሥቱ ወንበር ቀረብን ያሉ ናቸው። ለውጡን ሊደግፉ ሲገባ ለውጡ ተቀልብሶ ለእነሱ የቀይ ምንጣፍ አሸሼ ገዳሜ እንዲውል ነበር ያለሙት። መከራው ይሄው ነበር። ቢሰጣቸው እኮ ለግማሽ ቀን አይችሉትም። ምክንያቱም ትንፋሻቸው ያጠረ፤ ዓይናቸው የጠበበ፤ ትእግስት ያልፈጠራላቸው፤ ሃሳብ ማፍለቅ እርማቸው የሆነ ስለሆኑ …

አቤቶ ጊዜ ሲለግምም ሲቃናም ...

ምስል
ንጉሥ ሆይ! አቤቶ ጊዜ። „ጥበብ በጎዳና ትጮኻለች።“ (ምዕራፍ ፩ ቊጥር ፳ ) ከሥርጉተ©ሥላሴ (11.07.2018) (ከገዳማዊቷ ሲዊዝ።) ጊዜ ሲያልፍ ጊዜን ተክቶ ጊዜ ሲያከትም ራሱን ጊዜን አትግቶ ግን ሲክድ እራስን አስከድቶ ሲመጣም ሲሄድም ጊዜ አውክቶ ተፍነክንኮ ተፈልቀልቆ … በሰነፎች አሽካክቶ በልባሞች ተመስጦ በማስተዋል ተከንድቶ። ጊዜ ሆይ! የደላው …. ልግመኛው ባለዱላው ሲመጣም ሲሄድ የማይደከመው አይታክቴው ሲያሰኘውም ከትክቶ ሲያሻውም አንኮታክቶ በስልት ማጭድ አዘናግቶ ጌዜ ጌታው ሁሉን ነስቶ፤ ሽው ይላል ኩፍስን አፍንድቶ። አቤቶ ጊዜ እንዲህ ነው … … ቅነኛነት ሲያሻውም ሁሉን አድርቶ መንፈስ ገዝቶ ካለዲካ አበርትቶ ሁሉን በመለክ አብራርቶ አብርቶ። መልካሙነን አከማችቶ ህሊናውን አጋብቶ ለጥበቧ ነፍሱን ሰቶ ጊዜ ደጉ አንቶፈንቶን ትቶ ገመናው ጋልልጦ ቁጥቋጦ አሳጥቶ ፍልስ አድርጎ አሰምቶ። የቀና ለት እጬጌው ጊዜ … በስነደዶ ሰብዞ በዛጓሎ አከናንቦ በስንድዷ አሰናድቶ ጥልፍ ሆኖ አስጠልፎ ጥበብ ሆኖ አስጠብቦ ምልዕትን መግቦ። ጊዜ ሆዬ አዘምኖ አዝምንምኖ … ሁሉ ሰጥቶ ብህትናን ለግሶ ፍቅርን ወርቦ ቀድሶ ትንሳኤን አቋድሶ።  እቴ እሱ … አያ ጊዜ ንጉሥ ጊዜ … ሲያስፈልገው ኖን ጋብዞ የሳቀ ለት የስን አሳቅፎ ሥርዬት ሆኖ ነፍስ ዘርቶ ሐሴት ሆኖ ሰናይ ቀብቶ በአናባቢው አስነብቦ ይሸልማል ድሮ ኩሎ ዕሴት ሠርቶ ሰው መሆንን አበጅቶ ባጅቶ። ዐጤ ጊዜ ሲመርቅ … አሜኑን አስቀድሞ በቅኔውም አሳምሮ ማህሌቱን በሚስጢራት አሰድምሞ አሳርጎ ማጫውንም አ

በቦርቅቅ ቀልድ፤

ምስል
የአንባርጭቃ እንፉቅቅ። „ሰነፎች ግን ጥብበንና ተግሳጽን ይንቃሉ።“ (ምዕራፍ ፩ ቊጥር ፯ ) ከሥርጉተ©ሥላሴ (11.07.2018) (ከገዳማዊቷ ሲዊዝ።) ጠቅ ጠቅ ብትክት በቀቅ በበቀን ብርክርክ ሰክሰክ ፍርክርክ፤ ሸክሸክ ቅልሽልሽ ፈቅፈቅ ሽውድውድ፤ ተክተክ ሙርቅርቅ ብቅብቅ በጥልቅ ድብልቅልቅ ጥወልውልልልልልልልል .... ብንብን ትድለቅ ትንትን ትቀልድ በቦርቅቅ፤ የዙርግንብ ያልተገራ ቅጥ የጆፌ ቅይጥይጥ የአንባርጭቃ እንፉቅቅ። ·        ሥ ጦታ ለልቆች ልቅ። ·        ሰ ዓት። መንፈቀ ሌሊት 01.27   ·        ቀን 11.07.2018 ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጢር! የኔዎቹ ኑሩልኝ። ማለፊያ ጊዜ።

እንትንኛ!

ምስል
እንትንኛ! „አላዋቂዎች ከጥበብ መራቅ ይገድላቸዋልና ሰነፎችም ቸልተኛ መሆን ያጣፋቸዋልና።“ (ምሳሌ ምዕራፍ ፩ ቊጥር ፴፪) ከሥርጉተ ©ሥላሴ (11.07.2018) (ከገዳማዊቷ ሲዊዝ።) እንትንኛ እንቶንኛ የከትከት ሁነኛ። ምንትሶኛ ቅብጥርሶኛ የከትከት ማህበርተኛ። እንቶ ፎንቶኛ ዝልቦኛ ቀበኛ የከትከት ዘበኛ። ቀማኛ መስቃኛ ዕለትኛ የከትከት ዞበኛ። ·        ሥ ጦታ ለልቆች ልቅ። ·        ሰ ዓት። መንፈቀ ሌሊት 01.18   ·        ቀን 11.07.2018 ·          ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጢር! የኔዎቹ ኑሩልኝ። ማለፊያ ጊዜ።

ፍልሶሽ።

ምስል
የዕምል ፍልስ። "እናንተ አላዋቂዎች አስከ መቼ  አላዋቂነትን ትወድዳላችሁ? ፌዘኞች ፌዝን ይፈቅዳሉን? ሰነፎች ዕውቀትን ይጠላሉን?" (ምዕራፍ ፩ ቊጥር ፳፪) ከሥርጉተ ©ሥላሴ (11.07.2018) (ከገዳማዊቷ ሲዊዝ።) ግትልልትትትትትትል ግምልልልልልልልምምል ዝክትልልልልልልትል ልም ግምል። ሁልጊዜም ግትልትል ምንጊዜም ግምልምል የሰርኩ ዝክትልትል የንፈስ ዲል። ልል ብል ዝልዝል ዝል ዝል የዝምብሎ ዕምል። መልምልልልልልል ፍልፍልልልልልፍል ፈረፈር ለፈረፍር ግርግርግገርግር የሸር ግርርርርር የተንኮል ግግር ግርር። ሰፍ! ለተንሳፈፍ ሳፋ ስፍስፍስ በሙቅ ላይ ፍስስ የቅብጥ ቅልጥ ግምስ ቆይቶ ደግሞ አፍልስ። ምስምምስ ምስምስስ ስስስስስስስስ ብልተ ስስ መቋደሻው የሴራ ቡድስ። የተራራ ግርድስ ቡድስ ቡድስድስ የሃሳብ አዟሪት ግንድስ የለጠፍ ቁሮ ቡርድሰድስ የቁልል ቆሞስ ግርድስ። ፍልስ! ·        ሥ ጦታ ለልቆች ልቅ። ·        ሰ ዓት። መንፈቀ ሌሊት 00.57   ·        ቀን 11.07.2018 ·          ኢትዮጵያዊነት ፈተናን አሸንፎ የተፈጠረ ሚስጢር! የኔዎቹ ኑሩልኝ። ማለፊያ ጊዜ።

የኳስ ዊዲንግ ሻውር ምዕራፍ አንድ።

ምስል
ፈረንሳይን ያዬ ዛሬ ። 1 ለባዶ ቤልጀምን። „ምሕረት እና ዕውነት ከአንተ አይራቁ በአንገትህ እሰራቸው።“ (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፫) ከሥርጉተ ሥላሴ 10.07.2018 (ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ) ሜዳው ጭር ብሏል። ትንሽ እንደ ማኩረፍም ድንቡልቡሊት ሆናለች። የሠርጓን፤ ጠመልሱን፤ የቅልቅሉን፤ የማጫውን፤ የዊደንግ ሻወሩን የመረጠቸው ባዕትን ቅዳሜ ምሽት ኮከብህ አልገጠመም ብላ ስለሸኝች። ዛሬ የድንቡልቡሊት ዊዲንግ ሻውር የመጀመሪያው ዕለት ነበር። ምዕራፍ አንድ እንደማለት። ስለምን ሜዳው በጭርታ ተማታ? የራሺያ የዋንጫ መንፈስ ስለኮበለለ። የሆነ ሆኖ የዛሬ እግር ኳስ ጨዋታ የመጀመሪያው ፈረቃ ውድድር ካስን ነው የሚባለው። በዘንድሮው የእግር ኳስ ጨዋታ ራሺያ ጋር የነበሩ ግጥሚያዎች ፉክክራቸው እጅግ ዘመናዊ ነበር።  ከዚያ ውጪ እኔ በተከታተልኳቸው ጨዋታዎች እልህ አስጨራሽ የሚባሉ ነበሩ ለማለት ብዙም አልደፍርም። ኮሎንብያ እና ጃፓኖች ጥሩ ነበሩ። የግብጽና የራሺያ ግን የፋይናል ይመስል ነበር።  የኮራዚ እና የራሽያም እንዲሁ። ድንቁ ነገር የግብጽና የራሺያ ጨዋታ ገና የፊፋ የ2018 ጨዋታ አህዱ በተባለበት ሰሞናት ስለነበር ደረጃው ከጠበቅኩት በላይ ከፍ ያለ ነበር። ግብጽ ሳይቀጥል ቢቀርም እስከ አለፈው ሳምንት ድረስ ራሺያ ባገኘው ልምድ ተበረታቶ በሙሉ ደጋፊዎቹ የጀርባ አጥንትም ተጋዞ በጥንካሬው ቀጥሎ ተወዳዳሪዎቹን በሚያሰድምም ብቃት እያሸነፈ፤ ታዳሚዎችን እያስጨበጨበ ቀጥሎ በኮራዝን እልህ አስጨራሽ እጅግም አስገራሚ ጨዋታ በአገሩ በራሺያ ተስዶ በተመልካችነት እንዲቀመጥ ተገዷል። እርግጥ ነው ያን የመሰለ ብቃት ከመባቻው የነበረው የእኛው ወዛችን አፍሪካዊ መሃምድ ሳለህ የነበረበት