ዝቅዝቅ ቁንዳላ!
እንኳን ደህና መጡልኝ። ዝቅዝቅ ቁንዳላ! „ ምንም እንኳን በለስም ባታፈራ፣ በወይን ሐረግ ፍሬ ባይገኝ፣ የወይራ ሥራ ቢጓል እርሾችም መብልን ባይሰጡ በጎችም ከበረት ቢጠፉ ላሞችም በጋጥ ውስጥ ባይገኙ እኔ ግን በ እግዚአብሄር ደስ ይለኛል፤ በመዳህኒቴ አምላክ ሐሤት አደርጋለሁ። “ ትንቢተ ዕንባቆም ምዕራፍ ፫ ቁጥር ፲፯ ቁጥር ፲፰ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie ከእመ ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። · ጠብታ የኔዎቹ አዱኛዎቼ እንዴት አላችሁልኝ? እኔ አምላኬ ክብሩ ይስፋ ይንሰራፋ ደህና ነኝ። ለዛሬ የመረጥኩት ቃለ ወንጌል የመከራ ወጀብ መቋቋም የሚያስችል የህይወት መንገዴ ነው። ቤተሰቦቼ የሥርጉተ ንብረት ይሉታል። አዎን የመንፈስ እርስቴ ነው። በዚህ ቃለ ወንጌል አስተምህሮ ተስብሬ ሳልወደቅ፤ ግራቀኝ የማዕበል ሸክሙን፤ የመንፈስ ጭነት ቁሩን እና ሃሩሩን አደላድዬ እና አስመችቼ አስደስቼም የቅዱሱን ሰማዕት የወንጌል አርበኛውን የሐዋርያው ጳውሎስን „የይበቃኛል“ ምህንድስና ምራኝ ብዬ በሙሉ ሰብዕና፤ በሙሉ ሞራል፤ በሙሉ መንፈሳዊ አቅም በተፈጠርኩበት ልክ እና ቁመና መኖርን ደስ ብሎት እንዲኖር የተፈቀደበት ታላቅ የህይወቴ ክፍለ አካል ነው። ዛሬ ላለው እርእሴ የመረጥኩበት ወሳኝ ጉዳይም ስለአለ ነው። · እፍታ። ዛሬ ቅዳሜ ነው። ብራ ነው። ግን ጸጥታው ገኖ ወጥቷል። እናም ዛሬ ልሠራ ያሰብኩትን ጉዳይ ተግ አድርጌ እነሆ እናንተን አገኝ ዘንድ ወደድኩኝ። ቀደም ባለው ጊዜ ጉዳዩን አንስቼ በሳተናው ድህረ ገጽ ጽፌበት ነበር ስለ አቶ አሰማህኝ አስረስ። አሁን ሰሞኑን ደግሞ ያ የጻፍኩበት ነፍስ በአማራ የብዙሃን