ልጥፎች

ራዲዮ ጸጋዬ 01.04.2021 ላይፍ ከ15.00 -16.00።

ምስል
  • ዕለተ ሃሙስ ማዕዶት አሰጋሪው በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ህይወት አዝመራ ለራህብ የሚራራ። "የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል እግዚአብሔር ግን አካሄዱን ያቀናለታል" (ምሳሌ 16 ቁጥር 9) ዛሬ አሰጋሪው ሃሙስ ነው። ማዕዶተ ጸጋዬ። ጭምት ቀኔ ነው። የጠቅላዩም የግብረ ኃይላቸውም መንቦጫቦጭ ታዳሚው በእጅጉ እንደ ተሻሻሉ አድርጎ ስላዬው ነው። እያንዳንዱን ነገር ከሥሩ ለምን የሚል ጥያቄ አንስተን መመለስ ይገባል። ፡ወደው አይደለም ኦነጋውያኑ ሰሞኑን „ከሰው እንበላለን፤ ከእነቀረጥፋለን፤ ከእንሰብራለን ወደ“ „ሰቦያውያን“ ነን በቅጽበት የተለወጡት። ተበጥብጠዋል። ተፍረክርከዋል። የጠቅላዩ ቢሮ ተንጧል። ተመስገን ነው። እንዲህ የሚያርድ ቅዱስ መንፈስ ሲፈጠር። • ራዲዮ ጸጋዬ። የጸጋዬ ድምጽ ራዲዮ እአአ በ2008 በሲዊዘርላንድ ዙሪክ ከተማ የተመሠረተ ነው። ራዲዮው በወር ሁለት ጊዜ በዕለተ ሃሙስ ከ15.00 -16.00 ሰዓት በአማርኛ ቋንቋ ዝግጅቱን ያቀርባል። ዛሬም ላይፍ ላይ መጋቢትን እንኳን ደህና መጣህ ይላል። ሰዓቱ ሲደርስ አስቀድሜ ከ10 ደቂቃ በፊት ሼር አደርጋለሁኝ። የሌላ አገር ዝግጅት ስለሆነ ያን ታግሶ ማደመጥ ይገባል። ምክንያቱም ቆራጣ እንዳይሆን። ላይፍ ማደመጥ ለማትችሉት ቅኖች ደግሞ አርኬቡ ይህ ነው። https://www.lora.ch/sendungen/alle-sendungen?list=Tsegaye በተጨማሪም በራሴ ዩቱብም እለጥፈዋለሁኝ። https://www.youtube.com/channel/UCJEQXw86u_NG4A1FVC1j2qg... እግዚአብሔር ይስጥልኝ። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 01.04.2021 ጎዳናዬ ጸጋዬ እና መክሊቴ ነው።

የመሆን አዝመራ።

ምስል

ጠቅላይ ሚኒስተር አብይ አህመድ ሰብዕናቸው አሳቻ ነው።

ምስል

"የምድራችን ዕውነት ይህ ነው" ከጋዜጠኛ ብርሃኑ ተክለ ያሬድ።

ምስል

ሰልፉ፡- ስለ ገደልኸን እናመሰግንሃለን ነውን?

ምስል

ጭምቱ ለሁሉም አልጋው አማራ።

ምስል
  ማዕዶተ ሰባዕዊነት ለዛውም በሰንበት። ዕለተ ሰንበት ማዕዶተ ርትህ ሰባዕዊነት። በከበቡሽ የቁራሽ እንጀራ ብራና በቢሆነኝ የተብራራ ብራ በሰብለ ህይወት አዝመራ ለራህብ የሚራራ።   „ የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል እግዚአብሔር ግን አካሄዱን ያቃናለታል። " ( ምሳሌ 16 ቁጥር 9) • ጭምቱ ለሁሉም አልጋው አማራ። ዘመን - ተዘመን፤ ወቅት - ተወቅት፤ ሂደት - ከሂደት፤ ታሪክ - ከታሪክ፤ ትውፊት - ተትውፊት፤ ዓመት - ከዓመት፤ ወራት - ተወራት፤ ሳምንት - ተሰማንት፤ ቀን - ተቀን አንድም ዕለት ወቀሳ አብርቶለት የማያውቀው የአማራ ህዝብ መከራውን ተሸክሞ ኢትዮጵያንም ከእነመከራዋ ተሸከሞ አለ እንዳለ። ትናንትም ዛሬም። በአማራ ሥም የተደራጁት ሁሉ የሚታገሉት ለኢትዮጵያኒዝም ነው።   በኦሮሞ፤ በአፋር፤ በትግሬ ወዘተ … ሥም የተደራጁት ደግሞ ለራሳቸው ማህበረሰብ ነው። ጠቀመም ጎዳም። አማራ ሲደራጅ ኡኡ ! ተባለ። የተደራጀበትን ዓላም ግብ አይደለም መከራውን ማስታገስ ሳይችል የኢትዮጵያን መከራ ለመሸከመ ቆረጥ ቆረበበትም። ጎዳናውን በዛ ጠረገ። የኦሮሙማ አስተዳደር ተቀምጦ „ ኢትዮጵያን አትንኳት ? “ ከአማራ ድርጅት የሚወጣ የወል ድምጽ ነው። ይህን ሚስጢር የሚያነብ፤ የሚተረጉም፤ የሚያመሳጥር አቅም ያለው ሙሴ እስኪመጣ ድረስ ድሉን አማራ አይገኝም። አማራን በልኩ የተረዳ ተቋም የለም።   አማራ አማራ ሆኖ መታገሉን እራሱ ፈጽሞ አላወቀበትም። አልገባውም የተደራጀበት ዓላማ እና ግብ አያውቀውም።