ልጥፎች

ፈጣሪ አምላክን ስለ ፍጥረቱ ሚስጢራት አትዳፈሩት።

ምስል

Unity Einheit አንድነት።

ምስል

No War

ምስል

ዬሞት ተማህጽኖ፣ የስቃይባለተስፋ።

ምስል
ዬሞት ተማህጽኖ፣ የስቃይባለተስፋ።     ምን እና ለምን ስለምንስ። ምን አድርገን ተገኜን??? ጭንቀት ያነሰን መሰለወትን? መሬት ደብድበው ማት አውርድ ብለው መና ለቤተ እግዚአብሄር ዬሚልኩ መሪ ነበሯት። ኢትዮጵያ። ጠቅላይ ሚኒስተር አብይም በድምጽ ያገኙትን በትረ ሥልጣን በደም ጎርፍ አጥለቀለቁት። እኛ ቋያ ላይ ያሉ ቅኔወቻችን ነገን እንዲዩ እንዴት ዞር ሊሉ ይችላሉ እያልን እንጨነቃለን ህግ በሌለበት አናርኪዝም በሰፈነበት ባዕት፣ ባረገረገ ዙፋን ልቀቀል ብሎ መፍቀድ ሥምዬለሽ ማት ነው።።።።።።። ውጭ አገር እንደሚሰለቻቸው አውቃለሁ። ግን ይህም መከራ መቀበል ነው። እናቴ አዘውትራ ፃድቅ ትለኝ ነበር። የቀረብኝን ነገር ሁሉ ኡስባ። ፆምም ሲመጣ የሁልግጤ ፆሚነሽ እኮ ትለኝ ነበር። ከሚወዱት ባተሌነት መለዬት መከራን ፈቅዶ መቀበልም ነበር። "ዬቤትህ ቅናት በላኝ።" ዛሬ ምዕራፍ ዘጠኝን ልጀምር ሃሳብ አልነበረኝ። ሦስት ሃሳቦች ሲሞግቱኝ አድረዋል። አንዱ በቤተሰብ ጉዳይ ነው። ሁለተኛው ውሳኔ ነው። ባርች ሆይ ይቅርታ አድርጊልኝ። ሰላም ስጧቸው ቢያንስ አንቺ በመልካምም ቢሆን ሥማቸውን እንዳታነሺ ብለሽ የህማማት ዋዜማ ቃል አስገብተሽኝ ነበር። ይህም በመሆኑ ያዘጋጁት ዬሽግግር ሰነድ በማን እና በምን አመክንዮ እንደ ተጨናገፈ ስገልጽ ኢዴፓ እያልኩ ነበር። የሆነ ሆኖ አሁን ሞት ውሰደኝ፣ ጭንቀት እና ስቃይ ራዕዬ ይሁን ብለው ሲወስኑ ዝም ልል ህሊናዬ አልፈቀደልኝም። ፈጽሞ። ላም እረኛ ምን አለ ዬእኛ ፖለቲከኞች ድርቅ ዬመታው አመክንዮ ነው። የብዙ ነገር ውድቀት፣ የብዙ ነገር ኪሳራ ዬሚነገረው ስለማይደመጥ ነው። ላደለው ንግግር ብቻ አይደለም ዬሚደመጠው። ፀሃይ አድማጭ ትሻለች። ንፋስ አድማጭ ይሻል። ተፈጥሯዊ ወጀብ አድማጭ ይሻል። የወፎች ዜማ አድማጭ ይሻል መ

#የኢትዮጵያ_86ቱ ብሄር ብሄረሰቦች መጠሪያ ስም:-

ምስል
አቶ መላኩ ደጀኔ ዬተገኜ ነው። ይህቺ ኢትዮጵያ ትናፍቃኛለች።      ለጠቅላላ እውቀት #የኢትዮጵያ_86ቱ ብሄር ብሄረሰቦች መጠሪያ ስም:- 1. አማራ 2. ኦሮሞ 3. ትግራዋይ 4. ሶማሌ 5. አፋር 6. ሲዳማ 7. አገው 8. ዎላይታ 9. ከምባታ 10. ሀዲያ 11. ጋሞ 12. ጉራጌ 13. ኢሮብ 14. አርጎባ 15. ቱለማ 16. ስልጤ 17. ሺናሻ 18. አኝዋክ 19. ኑዌር 20. ሀመር 21. ኩናማ 22. ጉምዝ 23. በርታ 24. በና 25. አሪ 26. ሙርሲ 27. ቡሜ 28. ካሮ 29. ፀማይ 30. ኮንሶ 31. ዳሰነች 32. ቦረና 33. ጋብራ 34. አላባ 35. አርቦሬ 36. ባጫ 37. ቤንች 38. ባስኬቶ 39. ቡርጂ 40. ጫራ 41. ጋዋዳ 42. ጌዲኦ 43. ጊዶሌ 44. ጎፋ 45. አደሬ 46. ከፊቾ 47. ኮንታ 48. ኒያንጋቶም 49. ናኦ 50. ቀቤና 51. ሱርማ 52. ጠንባሮ 53. የም 54. ወርጂ 55. ዲዚ 56. ዶንጋ 57. ዳውሮ 58. ዲሜ 59. ምዓን 60. ኮሞ 61. ማረቆ 62. ሞስዬ 63. ኦይዳ 64. ቦዲ 65. ፈዳሼ 66. ኮሬ 67. ማሌ 68. ማኦ 69. መሰንጎ 70. መዠንገር 71. ቀዋማ 72. ቀጨም 73. ሸኮ 75. ዘየሴ 76. ዘልማም 77. ሽታ 78. ቤተ እስራኤል 79. ማሾላ 80. ኮጉ 81. ድራሼ 82. ገባቶ 83. ጌዲቾ 84. ብራይሌ 85. ሙርሌ 86. ኮንቶማ .... ናቸው። ************************ ምንጭ - የኢትዮጵያ ታሪክ፣ Amsalu Getu ኢትዮጵያ በትገነጠል 86አገር ይወጣታል  

ኢትዮጵያ ምን ትፈልጋለች? አቅጣጫችን አዬሩ ምን ይሽታል? ምዕራፍ ዘጠኝ።

ምስል
  ኢትዮጵያ ምን ትፈልጋለች? አቅጣጫችን አዬሩ ምን ይሽታል? ምዕራፍ ዘጠኝ።     "መለዬትን የሚወድድ፦ ምኞቱን ይከተላል፥ መልካሙንም ጥበብ ሁሉ ይቃወማል።" (መጽሐፈ ምሳሌ ምዕራፍ ፱፰ ቁጥር ፩) አመክንዮ ምን ይናፍቃል? እኛስ? እኔስ? ከአኔ ይጀመር። እሺ። ድካም እና ዬአቅም ፍሰት ለስኬት ሊሆን ይገባል። ትናንት ባልተደራጀ የትግል ፍሰት ሲኦል ውስጥ ተቀርቅረናል። አውራ ነን ያሉትም አውራ መሆን ተስኗቸው የኦነግ አንጋች ሁነዋል። አሁንም ያ እንዳይደገም በጠራ መስመር መጓዝ ግድ ይላል። እና። እኔ እምታገልለት ወሳኝ አመክንዮ። 1) ዬጎሳ ፖለቲካ በዓለም አቀፍ ደረጃ እንዲታገድ። 2) ፀረ ሰው፤ ፀረ ተፈጥሮ፤ ፀረ ታሪክ፤ ፀረ ዜግነት የሆነው የአልባንያ ሶሻሊስት ዬዞግ ግዑዝ መንፈስ ጋር የተቃቀፈው ህገ መንግሥት እንዲታገድ። 3) ኢትዮጵያን ሊመራ የሚችል ሰዋዊ፤ ተፈጥሯዊ ግብረ ኃይል ዕውቅና አግኝቶ አመራሩን እንዲረከብ። 3.1 አሁን ያለውን ሥርዓት በኃይል መደምሰስ የሚለውን አልስማማበትም። 3.2 በምርጫ መቀዬር ይቻላል የሚለውን አልስማማበትም። 3.1 በኃይል ማስወገድ ስልጡን መንገድ አይደለም። በተጨማሪ ነገን አጎሳቋይም ነው። ዛሬንም ዬሚገድል። መስዋዕትነቱን ዬሚያከብድ። አቅም ዬሌላቸውን ዜጎችም ለፈተና ዬሚዳርግ።ለቀጣይ ሰዓታት ዬነፍስ ማሳደሪያ ዬሚሆን ዬሌላቸው፤ ሊለምኑ ያፈሩ ሚሊዮኖች፤ አልጋ ላይ ያሉ ወገኖች፤ ህፃናት ብዙ ችግርን ዬምታስተናግድ አገር ይህ ተመራጭ አይደለም። 3.1.1 በምርጫ። ይህን በጀርመንኛ ምርጫ በሰላም ተጠናቀቀ ሲባል ጽፌዋለሁ። አጣዬ ስድስት ጊዜ ተቃጥላ፤ ሽዋ ሮቢት፤ ሻሸመኔ፤ ዝዋይ፤ ሃረር፤ ጅማ፤ ነደው፤ ሚሊዮኖች በገፍ ተፈናቅለው ከደቡብ እስከ ማዕከላዊ ጎንደር፤ በጦርነት፤ በስጋት በጭንቅ ህዝብ ሌላ አማራጭ ዬ

ዓላማ እንኳን ተፈጠርክልኝ ብሎ ዬሚመርቀው አቶ ኤርምያስ ለገሰ። • ለዓላማው ፍፁም ታማኝ።

ምስል
  ዓላማ እንኳን ተፈጠርክልኝ ብሎ ዬሚመርቀው አቶ ኤርምያስ ለገሰ። • ለዓላማው ፍፁም ታማኝ።   ለእኔ አቶ ኤርምያስ ለገሰ ግድፈታቸው ሳይዝረከረክ ጠቅላይ ሚር አብይ እንዲመሩ የተጋበት ዓላማው ነው ብዬ አምናለሁኝ። መብቱም ነው። አያደናግር ነበር በቀደመው ጊዜ ስሞግተው የነበረው። ኦህዴድ መራሿ ኢትዮጵያም ናፍቆቱ ናት ብዬ አምናለሁ። ይህም ሙሉ መብቱ ነው። አማራ ለሞቱ ግን ተኝተህ በለኝን ከዝኖ የያዘበት ስልቱ ያመኝ ነበር። ሰሚም ዬለም። ስንት ሰው ፈዞ፦ ደንዝዞ፣ ስንት አቅም ብን ብሎ ተፍረክርኮ ቀረ? "ዬቤትህ ቅናት በላኝ።" #ጠብታ ። አሁን ወጀቡ ረብ ብሏል። የጎሸውም ጠርቷል። ስለዚህ ሃሳቤን በሰከነ ሁኔታ ማቅረብ ፈለግሁኝ። አቶ ኤርምያስ ለገሰን ኢሳት መስራት ከጀመረበት ወቅት ጀምሮ አዬር ላይ አውቀዋለሁ። በደጉ ሳተናውም በሁለት ፁሁፎቼ ሞግቸዋለሁኝ። በተጨማሪም በባልደራስ እስር እና ያራምደው በነበረቀቀው ዬንደት ስልቱም በተከታታይ ፌስቡኬ ላይ ሞግቸዋለሁኝ። ሂደቱ በጥዋቱ ነበር የገባኝ እና። ከዛ በተረፈ ከህወሃት ሥልጣን ስለምን ዓላማ እንደለቀቀ፤ ሰብዕናውን ለአምስት ተከታታይ ዓመት ልክ እንደ አቶ ጃዋር መሐመድ አጥንቸዋለሁኝ። ምክንያቴ ሁሉም በዬቀለሙ ምን አስተዋፆ ሊኖረው ይችላል በሚል አርቄ ሳይሆን አቅርቤ የእኔ ብዬ አጥንቸዋለሁኝ። የፖለቲካ ድርጅት ተከፋይ ቋሚ ሠራተኛ መሆን እና ተምሮም ፖለቲካ ሳይንስን ዕድሉ ከሌለ የሰፋ ልዩነት አለው። በዚህም የዳበረ የፋንክሸነሪ ተመክሮ አለው። ከህወሃት ጋር መሥራቱ ከልጅነት እስከ ዕውቀት ከጫካ እስከ እስር ቤት ከእስር ቤት እስከ ስደት በነበረኝ ፀረ ህወሃት እና ባልተለወጠው አቋሜ ላይ ሆኜ አቶ ኤርምያስን ከህወሃት ጋር ሰራ የሚለው ወቀሳ ያመኛል፤ ለዚህ ተልዕኮም እስከ መጨረሻው ተባባ

ጉበትዎ እንደተጎዳ የሚነግሩዎት 10 ምልክቶች

ጉበትዎ እንደተጎዳ የሚነግሩዎት 10 ምልክቶች ጉበት በአካላችን ትልቁ ኬሚካል አመንጪ አካል ነው። ጥቅሞቹ ብዙ ናቸው። 3 ዋና ጥቅሞች አሉት። ባይል የሚባል ምግብን ለመፍጨት የሚያግዝ አረንጓዴ ኬሚካል ያመነጫል። በሰውነታችን ያሉ መርዛማ ንጥረ ነገሮችን ያጸዳል። የሰውነታችንን ሃይል ፍላጎት ላማሟላት ግሉኮስ ያመነጫል። ከጉበት አስፈላጊ ጥቅሞች አንጻር ጤናውን መከታተል ለሰውነታችን ጤና አስፈልጊ ነው። ጥሩ አመጋገብ፣ አካል ብቃት እንቅስቅሴ እና በቂ እንቅልፍ ማግኘት ለጉበት ጤና አስፈላጊ ነገሮች ናቸው። አልኮል እና ቡና ማብዛት የጉበታችንን ጤና አደጋ ላይ ይጥሉታል። ጉበታችን ሲታመም ህመሙ በብዙ ሰውነት አካላታችን ላይ ይንጸባረቃል። የተለያዩ የጉበት በሽታዎች አሉ። የተለመዱት ሲሮሲስ፣ ሲስቲክ ህመም፣ የጉበት ፋቲ ህመም፣ የሃሞት ጠጠር እና ሄፕታይተስ ናቸው። ጉበትዎን ሁሌ የሚንከባከቡ ከሆነ ጤናዎ ላይ ለውጡን ያዩታል። የጉበት ጉዳት ካለዎ አስቀድሞ በመታከም የመዳን እድልዎን ያሰፋሉ። የጉበት ጉዳት ምልክቶች 1) ማቅለሽለሽ እና ማስመለስ derneuemann / Pixabay ብዙ ሰው የማቅለሽለሽ ስሜት እና ማስመለስን እንደ አደገኛ የበሽታ ምልክት አይቆጥራቸውም። ያለምንም ምክንያት የማቅለሽለሽ ስሜት ወይም ማስመለስ ካጋጠመዎ የእኩላሊት ወይም የጉበት ህመም ያመላክታል። ስሜቱ የተሰማዎ ግን በምግብ መመረዝ ወይንም በሌላ የተያያዘ ህመም ከሆነ የጉበት ጉዳት የመሆን እድሉ ትንሽ ነው። የጉበት ጉዳት ያጋጠማቸው ሰዎች የማይለቅ የማቅለሽለሽ ስሜት ይሰማቸዋል። ይህ ስሜት የሚመጣው የጉበታችን መርዛማ ንጥረ ነገሮችን የማስወገድ ሃይል ስለተዳከመ ነው። የምግብ አፈጫጭ ለውጥም ማቅለሽለሽ እና ማስመለስ ያስከትላል። በየግዜው የማቅለሽለሽ እና የማስታወክ ስሜት ጤናችንን በከፍተ

"በነቀምቴ ለኦሮሞ ህዝብ ያስተላለፈው መልዕክት የአብይ ጭንቀት

ምስል
ዬማህበረ ኦነግ ውሎ አዳር። አንደበቱ ኦነግ ማይኩም ኦነግ ቅላፄውም ኦነግ። አማራን እንስበር ነው ተጀምሮ እስኪ ጠናቀቅ። "ከእንግዲህ አማራ ሁነህ ከአብይ ጋር በአንድ ቂጥ ካላራሁ ብለህ የምትጋጋጥ በግለሰብም ይሁን ቡድን ካለህ እርምህን አውጣ " "በነቀምቴ ለኦሮሞ ህዝብ ያስተላለፈው መልዕክት የአብይ ጭንቀት ሸኔን እንዴት መመለስ እንዳለበት ብቻ ነው የተጨነቀውጂ በፍጹም ለህዝቡ ሰላም፣ ልማት እና ብልጽግና አለመሆኑን በግልጽ አሳይቷል። ከተናገረው፥ እናንተ ወደኛ ኑ እንጂ ለሌላው በጭራሽ አታስቡ። ሌላው ያወራሉ፤ እኛ ግን ለኦሮሞ ነው የምንሰራው። እየሰራን ነው። ይሔ ብልጽግና የኦሮሞ መንግስት ነው። በዚህ ወቅት ስልጣኑ ከእጃችን ከወጣ በመቶ አመት ውስጥ አናገኘውም። በሰሜን በኩል ያሉት እያንገራገሩ ነው። እኛ ተደራጅተን እነሱን ማንበርከክ ካልቻልን እኛ ስልጣን ላይ ያለነው ብቻ ሳይሆን የምንጎዳው ኦሮሞ የሆነው ሁሉ ነው። በወለጋ በርካታ የተፈናቀሉ አሉ። እነዛ የተፈናቀሉት ለኛ የሚተኙልን ይመስላችኋል!? ሲልም በነቀምት ከተማ ከአራቱም ዞን ለተውጣጡ ለኦሮሞ ህዝብ ጥሪ አቅርበዋል። እናም ብዙ ጥያቄ በወለጋ ህዝብ ይነሳሉ። ለምሳሌ፦ በ1971ዓ.ም የትግራይ ህዝብ በዘመነ ደርግ በረሐብ፣ በጥይት እና በመከራ ውስጥ ሳለ፤ ወያኔ ነበር። አሁንም በወለጋ ያለው ችግር ይሔው አይነት ችግር ነው!? ኦሮሞ ሞተ!? ተሰቃየ!? ተራበ!? መንገድ አጣ!? ማብራት፣ ኔቶርክ፣ ትራንስፖርት፣ ትምህርት እና ጤና አጥቷል? መንግስት ይድረስልን ትላላችሁ!? መንገዱን ለማሰራት ኮንትራክተሮች፣ ባጀት፣ ማቴሪያል እና ሌሎች ቁሳቁሶችን ስንልክ ይዘረፋል፣ ይቃጠላል፣ ሰዎች ይታገታሉ፣ ይገደላሉ። ይህን ሁሉ ታድያ እየሆነ ያለው በደርግ ዘመን እንደወያኔ አይነት የ

#ለአማራ ህዝብ 40 ዓመት ሙሉ #ህማማቱ ነው።

#ለአማራ ህዝብ 40 ዓመት ሙሉ #ህማማቱ ነው። 27 ዓመቱ #ሥነ - ሥቅለቱ። #ዓራት ዓመቱ መቃብሩ! "ዝም ብዬ የመከራን ቀን እጠብቃለሁ" (ትንቢተ ዕንባቆም ምዕራፍ ፲፯ ቁጥር ፫) የተገለለ የገደለ የተሳደደ የተወገዘ የተሰቃዬ የተገፋ የተጨቆነ የታሠረ የመከነ የተሰደደ የተወጋ የታፈነ የተሠወረ የታገደ የተወገዘ ሰቆቃው አማራ! ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 21/04/2022 ተስፋችን አምላካችን ብቻ!