የልብህን ማድረስ የምትችለው በራስህ ጥረት ውስጥ ነው።
ሚዛን። „በአንደበቴ እንዳልስት መንገዴን እጠብቃለሁ፤ ኃጢያተኛ በፊቴ በተቃወመኝ ጊዜ በአፌ ላይ ጠባቂ አኖራለሁ አልሁ።“ መዝሙር ምዕራፍ ፴፰ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ 24.08.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። · ተ ያያዥ። ፈጽሞ ለውጥ የለም የሚሉ ወገኖች አሉ። ይህም መብት ነውና አከብራለሁኝ። ለውጥ ማለት ለእኔ ሰኔ 29 ወደ ሰኔ 30 ሲቀዬር ለውጥ ነው። መናገር በተዘጋበት ምድር መናገር ሲጀመር ለውጥ ነው። በዓዋጅ የታሠረን ብሔራዊ ሰንደቅዓላማ ሁለመናህ አድርገህ ካለ አጋጅ፤ ካለ ከልካይ ይዘህ ስትወጣ ለውጥ ነው። እንደ ጠላት ይታዩ የነበሩ የፖለቲካ ድርጅት መሪዎች ተፎካካሪ ይባሉ ተቀናቃኝ ኢትዮጵያ የእናንተም ናት እና የድርሻችሁን አበርክቱ ተብለው መጠዬቃቸው ይህ መጀመሩ በራሱ ለውጥ ነው። ለእነሱም አዲስ የተመክሮ ማሳ ነው፤ አዲስ የአስተዳደር እና የአማራር በር መከፈቻ ነው፤ አዲስ የአገልግሎት መስመር መከፈቱን ያበስራል። ህዝብ ከጠ/ ሚሩ ጋር ፊት ለፊት ጥያቄዎችን አቅርቦ ሲሞግት ማዬት ትልቅ ለውጥ ነው። ከጠረፍ እስከ ጠረፍ ያሉ ወገኖቼ ጋር የተደረገው ውይይት እኔ ኢትዮጵያ የገባሁ እስኪመስለኝ ድረስ በጥሞና ተከታትዬዋለሁ ብቻ ሳይሆን የትኛው ጥያቄ የትኛው ክልል ላይ ስለመሆኑ ሁሉ ልክ እንደ አንድ የትምህርት ክ/ ጊዜ አጥንቼዋለሁኝ። አልፎ አልፎም በእንባ ነበር የተከታተልኩት፤ ይሄም ለውጥ ነው እንደ አንድ የህዝብ አደረጃነቴ ቁምነገሬ ነው። ህዝብና መንግስት በቀጥታ የተገናኘበት አንድ ሃዲድ ነው ለእኔ። ከውጭ አገር የፖለቲካ አሳታፊነት ይልቅ በተሸላ ሁኔታ በተቻለ መጠን ሴቶችን ቦታ ለማስያዝ የሚደረገው ጥረትም ከወንዶች የፖለቲካ ዓለም ለኖርንበት የድቅ