ውሃ በቀጠነ ቁጥር መበርገግ አያስፈልግም።
እንኳን ደህና መጡልኝ። ውሃ በቀጠነ ቁጥር መበርገግ አያስፈልግም ። „ፈራህ አትፍራቸው።“ ትንቢተ ኤርምያስ ምዕራፍ ፩ ቁጥር ፲፰ ከሥርጉተ © ሥላሴ Sergute © Selassie 20.02.2019 ከእም ዝምታ - ሲዊዘርላንድ። · መንፈቀ ሌሊት - አንድ። እንዴት አላችሁልኝ የኔዎቹ ደህና ናችሁ ወይ? ዛሬ አንድ ህልም አዬሁኝ። አንድ የተዘጋ በር ተከፈተ። ከዛ የተዘጋ በር ሲከፍት ሜዳ አለው። ሜዳው ላይ ትንሽ ሳር በቅሎበታል። አንድ ሰው ከአቶ ሃይለማርያም ደስለኝ ጋር አለ። ያ ሰው ግን ግርዶሽ ጥሎበታል። እናም አቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ሳሩን ገፋ ገፋ አድርገው ከሉት። አቶ ሃይለማርያም ደስአለኝ ሳሩን ገለጥለጥ ሲያደርጉት በሰው ቁም ልክ የሆነ ጉድጓድ ተከፈተ። ከዛም አንድ ብረት በብረት የሆነ የተቆለፈ ትልቅ የብረት ሳጥን ወጣ። እንደወጣ ቀረብ ብዬ ላይ ስፈልግ በሌላ አቅጣጫ ከአንገቱ ላይ ራፊ ያደረገ አንድ እርቃነ ነፍስ የሆነ ከ9 እስከ 11 ዓመት ዕድሜ የሚሆን ታዳጊ ወጣት መለመላውን መጣ። ታዳጊ ወጣቱ ያልተገረዘ ነው። ታዳጊ ወጣቱ ዕብድ ነው። እሱ ሲመጣ እኔ ፈርቼ ቦታውን ለቅቄ ወጣሁኝ። ስወጣ ያ ሳጥን ሳይከፈት ነበር ... ህልሙ የውነት ነው። ፍቱት… ኢትዮጵያ መንፈቀ ሌሊት ላይ ነው ያለችው። · መ ንፈቀ ሌሊት - ሁለት። ያው የማለዳ ቁርሴ የሳተናው ድህረ ገጽ ነው። በርከት ያሉ ጹሑፎች አዬሁኝ። ትንሽ አነበብኩኝ። ስለ ጠ/ሚር አብይ አህመድ „ካህዲነት“ ጠንከር ያለ ጹሑፍ ወጥቷል። ሰለ ወዮልሽ አዲስ አባባም እንዲሁ። አሁን መፈናቀሉ ደግሞ ማህሉን እያመሰው ነው። ይህ በዚህ እንዳለ ትናንት ማምሻ ላይ ኦዴፓ አንድ ጠንከር ያለ መግለጫ አውጥቷ