ልጥፎች

ሎሬቱ ሰምቶ ይሆን? (ከጸሐፊ አቶ መስፍን ማሞ)

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ!  ሎሬቱ ሰምቶ ይሆን? “የሰው ልብ መንገድን ያዘጋጃል እግዚአብሄር  ግን አካሄዱን ያቃናለታል።” ምሳሌ ፲፮ ቁጥር ፱ መስፍን ማሞ ተሰማ ሠላም ለናንተ ይሁን! ቅኔያዊነት! ስለ ቴዎድሮስ ሹርባ ሎሬቱ ሰምቶ ይሆን? ከሰማ ንገሩን፤ ካልሰማም የምትችሉ ንገሩት፤ እኛ ግን ይህንን እንላለን። እነሆ ከ1868 እስከ 2019 (እአአ) በለንደን እንግሊዝ የኖረው የቴዎድሮስ ሹሩባ ሳይሆን የመይሳው መንፈስ ከመይሳው እናት ጋር አንድም ሁለትም እልፍም ሆነው ነው፤ ኢትዮጵያና ካሳ። በሹሩባው የገዘፈው ቴዎድሮስ ብቻ ሳይሆን ሽጉጡን የጠጣላት እናቱ ኢትዮጵያም እንጂ! ዓለም ከዓለም ጥግጋት እየተጠራራ አንጡራውንም እያፈሰሰ (ለእንግሊዝ የእርም ገንዘብ) እንደ ትንግርት ሲመለከተውና ሲደመምበት የኖረው የቴዎድሮስ ሹሩባን ሳይሆን በሹሩባው ቀጫጭን ፀጉሮች ላይ የተፃፈውን የ3ሺህ ዘመን የእናቱን ገድልና ታሪክ ጭምር እንጂ! እነሆ ለ150 ዓመት የአውሮፓን ሥነ ልቡና ያስጨነቀው - የቴዎድሮስ ሹሩባ መንፈስ - የዘመን ጉዞና ታሪክን ይዞ ከለንደን አዲስ አበባ (የእናቱ እምብርት) ተመልሷል። እናቱ ኢትዮጵያ ግን እንዴት ነበረች? እንዴትስ ናት? መይሳው ቴዎድሮስ ያኔ መቅደላ አናት የኢትዮጵያን ውርደት <በጠላት እጅ ወድቄ ከማይ> ብሎ ጥይቱን ሊጠጣ ሲዘጋጅ እንዲህ ብሎ ለእናቱ ነገረ። <ይልቅስ ተረት ልንገርሽ የተላከ ከእንግሊዝ ዘንድ፤ እጅህን ስጥ አለኝ ፈረንጅ እጅ ተይዞ ሊወሰድ፤ ምን እጅ አለው የእሳት ሰደድ? አያውቅም ክንዴ እንደሚያነድ? ሆኖም ጎስቌላ አልምሰልሽ የሚያዝንልኝ አልፈልግም፤ ጠላትሽን በክንድሽ እንጂ በእንባሽ ወዝ ባላሸንፍም፤ የልቤን ፍቅር በስተቀር የማወርስሽ ውል የ

ድላዊቷ ክብርት የባህል ሚነስተሯ ዶር ሂሩት ካሳ እና ቅብዕቸው!

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ!  ድላዊቷ ክብርት የባህል ሚነስተሯ ዶር ሂሩት ካሳ  እና ቅብዕቸው ! „ልባችሁን በመንገዳችሁ ላይ አድርጉ ወደ ተራራው ውጡ ብዙ ዘራችሁ  ጥቂትም አገባችሁ እንጨትም አምጡ፣ ቤቱንም ሥሩ እኔም በእርሱ ደስ ይለኛል፣  እኔም አሰግናለሁ፤ ይላል እግዚአብሄር። እናንተ ብዙ ተስፋ አደረጋችሁ፤ እንሆም ጥቂት ሆነ ወደ ቤትም ባገባችሁት ጊዜ እፍ አልሁበት“ ትቢተ ሐጌ ፩ ቁጥር ፯፱ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 23.03.2019 ከእመ ዝምታ ሲዊዘርላንድ። ·          ከመነ ሻው እስከ መዳረሻ። https://www.youtube.com/watch?v=fQxb2mpabNY&t=1s Ethiopia: ሰበር መረጃ - ኢትዮጵያ የአጼ ቴዎድሮስን ጸጉር ተረከበች | Emperor Tewodros II https://www.youtube.com/watch?v=_lvxb_jjAOw Ethiopia: ተወዳጁ ቴዲ አፍሮ የተገኘበት የአፄ ቴዎድሮስ ፀጉር ( ቁንደላ ) ደማቅ አቀባበል https://www.youtube.com/watch?v=YcVKFqCT57Y ቴዲ አፍሮ የተገኘበት ከ 150 አመት በኋላ የተመለሰው የአፄ ቴዎድሮስ ቁንድላ አቀባበል ላይ የተላለፈ መልዕክት https://www.youtube.com/watch?v=JsRHQTNL6W8 ዛሬ ተወዳጁ ቴዲ አፍሮን ሳቅ በሳቅ ያደረገው ንግግር በብሄራዊ ሙ ዚየም   እንዴት ቆያችሁ አዱኛዎቼ? ከሰሞናቱ ከዛ እዬራዊ ቁጣ ተመልሰን ከ14 ቀናት በኋዋላ ደግሞ  የ150 ዓመት ታሪክ በምልሰት እንቃኝ ዘንድ እዮር ፈቅዷል ። ከሰሞናቱ የአንግሊዝ መንግሥት የንጉሦስች ንጉ

ክቡር ሆይ ፈቀደዎት ቢሆንስ - ማስተባበያው ቢበቃስ? ሃሳቡ ሬሳ ነው።

ምስል
ማስተባበያው ቢበቃስ? „የሠራዊት ጌታ  እግዚአብሄር እንዲህ ይላል፤ … ልባችሁ በመንገዳችሁ ላይ አደረጉ“ (ትንቢተ ሐጌ  ምዕራፍ ፩ ከቁጥር ፭ እስከ ፮) ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 23.03.2019 ከእመ ዝምታ ሲዊዘርላንድ። ·        መነ ሻ!                                                   https://www.satenaw.com/amharic/archives/65396 ዶ / ር አብይ ፣ “ በአ / አኦዴፓ ያወጣው መግለጫ የለም፣ የግለሰብ መግለጫ ነው ” አሉ - በአያሌው መንበር። የቧልትም ዓይነት አለው። ·        መ ክፈቻ! እንደምን አላችሁ የኔዎቹ? ደህና ናችሁ ወይ? ዛሬ ብራ ነው ከዚህ። ሰሞናቱ ብራ ነበር። አልከፋውም። ገብያዎችም ደራ ብለዋል። ሞቅ ደመቅ እንደማለት። ብራ እጠበቀው የነበረው በአገረ ኢትዮጵያ ነበር። አሁን ግን ብራው ቀርቶ ደመናው ቢፈቀድ መልካም በሆነ ነበር። ጭፍግግ ያለው የከፋ ነገ በካቴና ታስሮ ብቅ እያለ ነው። የወንበሩ ባዶነት ከቀደመው ይልቅ አሁን ጎላ ደመቀ ብሎ ወጥቷል። እዬተውተረተረ ያለው የጠ/ሚር አብይ ካቢኔ መቆሚያውን እየሳተ ስለሆነ፤ አቅም አለው ብሎ ከሚያምነው ኮተት እያለ ስለመሆኑ ከዚህም ከዚያም የሚዘገቡት መረጃዎች ያመለክታሉ። መስሎት ነው እንጂ ያም ባዶ አዬር የተሞላ ፕላስቲክ ነው። ዕጣውን መጋራቱ ግን ያው የሚከዳው የ አማራ አምላክ ስላደረገው አብዝተን እንማሰገንዋለን።  ለነገሩ እኔ ከሀምሌ 19 ጀምሮ የወንበሩን ባዶነት በህልሜ ስለዬሁ እንደ ሰው ዬጊዜው ዝብርቅ ነገር ቢገርመኝም የወንበሩ ባዶነት ግን አልተጠራጠርኩትም ነበር። የመንፈሱ መጠለፉን በወቅቱ በስፋት ጽፌበታ