ልጥፎች

ስለምንፈልገው ነፃነት ዝግጁነት አይነሰን።

ምስል
ዝግጁነት። „ፌዘኞች ከተማቸውን ያቃጥላሉ፤  ጠቢባን ግን ቁጣን ይመልሳሉ።“ መጸሐፈ ምሳሌ ተግሳጽ  ምዕራፍ ፳፱ ቁጥር ፰ ከሥርጉተ ©ሥላሴ 06.08.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ። ·        መቅድ መ ሃሳብ። ተወዳጇ ፆመ ፍልስቲት መጣችልን። ፆመ ፍልሰቲት ቀኗ አጭር ግን እጅግ የተመስጦ እና የሱባኤ፤ የምህላ እና የሰጊድ፤ የተደሞ እና የትሩፋት ጾም ናት። ፍልሰቲት የውስጥ ሰላም ማስፈኛ ወቅትም ናት። አማና ይህን ጊዜ፤ ታች አምና ይህን ጊዜ፤ ከዛም በፊት ይህን ጊዜ ሃይማኖታዊ በሆኑ ጉዳዮች የሱባኤ ወቅቱን ውስጣችን ጥቁር ለብሶ ነበር የተከወነው። ተስፋችን በልዑል እግዚአብሄር ብንጥልም ከቀን ወደ ቀን እዬጠነከረ በመጣው ጭካኔ ምክንያት ተስፋችን፤ እምነታችን፤ ጽናታችን የፈተኑ እጅግ አስቸጋሪ ጊዜን አሳልፈናል። እነሆ ዘንድሮ በልዑል እግዚአብሄር ቸርነት እና ፍቃድ ብጹዕን አባቶቻችን፤ ሊቃውነት ቤተክርስትያን በአኃቲ ልቦና ሆነው ሱባያቸውን የሚይዙበት የተባረከ፤ የተቀደሰ ጊዜ ላይ እንገኛለን። ተመስገን! በውስጣችን ትፍስህት፤ ተስፋ፤ ማግስትን አስበን፤ መኖራችን የፈቀድንበት ወቅት ላይ ነን። ስለሆነም የ2010 ጾመ ፍስቲት ከወትሮው በተለዬ በውልዮሽ ማዕዶተ ፍቅር፤ በውልዮሽ ማዕዶተ መተሳሰብ፤ በወልዮሽ ማዕዶት መከባባር ፍለስቲት በጥልቅ የተመስጦ መንፈስ አምሮባት ትከወናለች ማለት ነው።  ተመስገን! ሳይሽ እወላለሁ ከልቤ አስቀምጬ ሳይሽም አድራለሁ አቅፍ አንተርሼ አወሳሳሻለሁ አድርሽኝ ለብሼ አንቺን እዬሳሳሁ ጀግንነት ወርሼ እንደ ወጣሁ አልቀር አይቀር እንደ መሼ፤ „አድርሽኝ“ ግጥም ለህትምት የበቃ ነው፤ ሁልጊዜም በጸጋዬ ራዲዮ ላይ እንደ ድርሳን የመግቢያ መዝሙሬ ነ

ዝም አትበሉ መንገርም ማናገረም መልካም ነው።

ምስል
ግዙፉ የግንቦት 7 ፈተና። „ደሴቶች ሆይ በፊት ዝም በሉ አህዛብም ሃይላችውን ያድሱ፤ ይቅረቡም በዚያን ጊዜ ይናገሩ፤ ለፍርድ በአንድነት እንቅረብ“ ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ ፵፩ ቁጥር ፩ ከሥርጉተ©ሥላሴ  05.08.2018 ከጭምቷ ሲዊዘርላንድ። ·       መራረነት ጣፋጭነትም የእግዜሩ ሰውኛ ናቸው። የዚህ ጹሑፍ ጭብጥ የሚመራቸው ይኖራሉ። ያው ሥርጉተ ሥላሴ እንደምትማራቸው ዓይነት። ግን ዘመኑ መራራን ማድመጥ አትራፊ ስለመሆኑ እዬታዬ ነው። መራራውን መናቅ ደግሞ የውድቀት መጀመሪያ ስለመሆኑም ዘመኑ ተመሰጠረበት። ከመራራዎቹ አምክንዮች ነው ዛሬ ላይ ትርፍ እዬተዛቁ የሚገኙት። ከ66 አብዮት ማግስት ነገረ አማራ በጥርስ የተያዘ ግን በመናጆነት የተቸነከረ ጉዳይ ነበር። የመፍትሄው ቁልፍ ግን ከነገረ አማራ ላይ የተነሳ መንፈስ ብቻ ነበር። ማለት አማራነት መራራነት ነበር ግን በራሱ አቅም ውስጥ ጎልቶ እንዳይወጣ ቁልጭ ያለ መድሎ ነበር። አሁንም አለ ትሉ ይሆናል ጊዜው ልጅ ነው እና የአብዩን መንፈስ በዚህ መንቀስ ብዕሬ አትደፍረውም። ላያቸውም የምፈቅዳቸው የጊዜ ሰንጠረዦች አሉና ...  ነበር ስል ግን አሁን የለም ለማለት አይደለም። አልተጀመረም ቀድሞ ነገር። ነገረ አማራ በፖሊሰ ደረጃ ነው ጭቆናውም፤ ግለቱም። ስለዚህ ተንስኤው የፖሊሲው መወገድ ብቻ ሳይሆን እጭ የሰሩ ጸረ አማራ እሳቤዎች ጊዜ ብቻ ነው ነቅሎ የሚጥላቸው። ዛሬ እንኳን በ እኛ አቅም ለተገኘ መባቻ የሚታዬውም፤ የመደመጠውም ድፍረት ማጣቱም እዬታዬነው።  ይህን መሰረት ለማስያዝ በራስ ውስጥ የበቀለ አቅምን በመገንባት ብቻ የሚገኝ ነው። ይህም መራራ ጉዞ ነው። አሁንም አማራነት መራራነት ነው። የትኛውም አካል  ለድል ካበቃ ወይንም መሬት የረገ

አለማወቅን በዕውቀት መቀበል መቻል።

ምስል
ጥሞና ስለህሊና። „ውኆችን በእፍኙ የሰፈረ ሰማይንም በስንዝር የለካ፣ የምድርንም አፈረ በመስፈሪያ ሰብስቦ የያዘ፤  ተራሮችን በሚዛን ኮረብቶችንም በሚዛኖች  የመዘነ ማን ነው?“ ትንቢተ ኢሳያስ ምዕራፍ ፵ ቁጥር ፲፪ ከሥርጉተ © ሥላሴ።  05.08.2018 ከገዳማዊቷ ሲዊዘርላንድ።  ·       መ ቅድመ ሃሳብ። የኔዎቹ ቅኖቹ ውዶቹ እንዴት ናችሁ? በዬወቅቱ አዳዲስ ፓርቲዎች፤ ውህደቶች፤ ህብረቶች ይፈጠራሉ። አዲስ ሁኔታ በተፈጠረ ቁጥር በመገላበጥ ወይንም በመመሰጥ አዳዲስ ሁነቶችን የተከተሉ በዬዘመኑ አዳዲስ ሊሂቃን፤ ታታሪዎች፤ ጋዜጠኞች፤ ተንተናኞች ይወጣሉ። አብሶ ፓለቲካ ድርጅት መሠራቾች ሊሂቃን ከወጡ በኋዋላ በመቀደም ይሁን በመሰበር የጀመሩትን ሳይጨርሱ ሲከሽፍባቸው በሌላ ሁኔታ ደግሞ አዲስ ዓላማ በአዲስ ሥያሜ ሌላ ውጥን ይዘው ይነሳሉ፤ ይህ የማያቋራጥ በዙር ተመለስ የታዬ ጉዳይ ነው ነገም ቀጣይ ነው። አብን እማዬውም ከዚህ አንጻር ነው። ከታጋድሎው መንፈስ ጋር አብሮ እንኳን መፈጠር አልተቻለውም አብን። እጅግ ዘግይቶ ለዛውም አስቸኳይ ጊኤዜ አዋጅን ተንትርሶ እና አዲስ ጠ/ ሚር መንፈስ ሲፈጠር ነው ከች ያለው። የነገ ቀጣይነት  ለሚለው ዋቢ የሚሆነው የድርጅቱ አመሰራረት ሁኔታ ወሳኝ ነው። ሞረሽ በቀደመው ፍልስፍና ቀጥሎ ቢሆን ኖሮ ዘላቂ ስኬቱ አንቱ በሆነ ነበር። ምክንያቱም አመሠራረቱ መርህ እንጂ ወጀብ ስላልነበር። ነገር ግን እሱም አንዛላለጠው እና ወደ ፖለቲካ ድርጅትነት የተለወጠበት አሰገዳጅ ሁኔታ የአማራ ተጋድሎ መምጣት ነበር። የተጋድሎውን መንፈስ ሳያጣጥም ነበር በሽሚያ ወደ ፖለቲካ ድርጅትነት የተለወጠው።  ዘላቂ ዓላማ ቢኖር ቀድሞውንም ሞረሽን በተረጋጋ ሁኔታ የፈጠረው መንፈስ