ልጥፎች

ይድረስ ለአቶ ጌታቸው ረዳ! (ከጸሐፊ አቶ መስፍን ማሞ።)

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  ይድረስ ለአቶ ጌታቸው ረዳ ! “አውቃለሁ ለኅጣእ ግን ደህንነት የለውም፤ በእግዚአብሔር ፊት አይፈራምና፤ ዘመኑ እንደ ጥላ አትረዝምም። ” መጽሓፈ መክብብ ፰ ቁጥር ፲፫ ከጸሐፊ አቶ መስፍን ማሞ ተሰማ ጥር 2011 ዓ/ም (ጃንዋሪ 2019) ሲድኒ አውስትራሊያ አቶ ጌታቸው ሆይ - ዕውን የነበረከት እስር ደንቆኃል? ወይንስ ነግ በኔ ታይቶህ ደብሮኃል? አዎ ባንተ ልኬት እነ በረከት በሙስናው ዝቅተኛ ወለል ላይ የሚገኙ ናቸውና የታሰሩበት ምክንያት ፖለቲካዊ ነው ብለሃል። (ይገርማል ደግሞ የዝርፊያቸውንም ልክ ታውቃለህ ማለት ነው?) ለማንኛውም እስራቸው ፖለቲካዊ መሆኑን ለማን ነው የምትናገረው? ለራስህ ከሆነ ዕውነት ብለሃል። አንተና በረከት ሞክሼህ ጌታቸውና ሁላችሁ በህወሃት አቁማዳ ውስጥ ሆናችሁ ከኢኮኖሚው በባሰ በፖለቲካው የሰራችሁትን ሰቆቃ ታውቃለህና! አዎ! እንኳን እኛ ዓለም በረከትን የሚያውቀው በዘር አጥፊነቱ <በናዚስት ጎብልስነቱ> ነው። ስለ በረከት <ናዚስታዊ ተግባር> (የኛን ዝርዝር ለጊዜው አቆይተን) የአውሮፓ ፓርላማን ስመ ጥር አባል ወ/ሮ አና ጎሜዝን ዋቢ እንሰጥሃለን። ክሱ ከምንጠበቀው ከፍታ ላይ እስኪወጣ <አይነኬው> በረከት <በኢኮኖሚም> ቢሆን መታሰሩ ወደ እናንተ መቅረባችን ነውና እኛ ደስ ብሎናል! ደግሞምኮ መንግሥት ነኝ ብሎ ሀገር መዝረፍ፤ የድሃ ጥሪት መግፈፍ ያስቀፈድዳል - በተዘረፈ ሀብትና ንብረት ክምችት መለኪያችሁ ወለልም ላይ ሆንክ ጣራ ላይ!! ዘንድሮ ከነ ጓ ዶችህ አይቀርላችሁም። ረስተኸው ከሆነ <እሳትና ጭድ> በሚለው የዘር ዕልቂት ፕሮፓጋንዳህ ትጠየቅበታለህ/

የሱማሌው ችግር የተፈታበት መንገድ እንደገና ታጥቦ ጭቃ - ዳጥ ላይ? ህም!

ምስል
ጭጎጎታማ ዳመና። „ሰማይ ጽድቁን ይናገራሉ፤ እግዚአብሄር ፈራጅ ነውና።“ መዝሙር ፵፱ ቁጥር ፲፮ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 23.01.2019 ከእመ ዝምታ። ጤናይስጥልኝ ውዶቼ እንዴት ናችሁ? ደህና ናችሁ ወይ። ዛሬ ብራ ነው። ብራ እወዳለሁኝ። በዛ ሰሞን ዘሃበሻ ስለ ሰብዕዊ መብት ጽኑ ተሟጋቹ አቶ ሙስጡፋ ዑመር ከሥልጣን የመልቀቅ ጥያቄ ሹክ ብሎን ነበር። መርዶ ነበር ለእኔ። ድክም እያለኝ ነበር ያዳመጥኩት። መረጃው ቀዝቃዛ ነበር ስቀበለው። ብርድ ብርድ ብሎኝም ነበር።  ዛሬ ደግሞ አንድ አጭር ውይይት ከአንድአፍታ አዳመጥኩኝ። እጅግ እማከብራቸው አክቲቢስት አቶ ጀማል ዲሪዬ ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ ነው። እሳቸው የፕሬዚዳንቱ የህግ እና የሰባዕዊ መብት አማካሪ መሆናቸው እጅግ ድንቅ ነገር ነው። በዚህ ደስ ብሎኛል። ግን ሊሰሩበት የሚገባው እርግጠኝነት ድጋፍ አልባ ነው። ብረት መዝጊያ የሆነ መንፈስ ያስፈልጋቸዋል። የሱማሌ ጉዳይ የተፈታበት መንገድ ከሁሉም አገር ውስጥ እርምጃዎች እጅግ የላቀው ነበር ማለት እችላለሁኝ።   ታጥቦ ጭቃ እንዳይሆን ግን ስጋት አይሏል። በውጭ ስንመለከተው የኢትዮጵያ ኤርትራን ጉዳይ ጉልሁ ማለት እንደምችለው ነበር ያን እርምጃ እኔ ያዬሁት የአቶ አብዲ ኢሌ በቁጥጥር ሥር መዋል እና የአቶ ሙስጡፋ ዑመር ወደ ሥልጣን መምጣት የታምር ያህል ነበር የተመለከቱከት፤ ተከታታይ ጹሑፎችንም በአጽህኖት ጽፌ ነበር። ለዛውም ማንም ያን ጊዜ ከቁብ የቆጠረው ባነበረበት ጊዜ ነው እኔ ተደሞውን ያስኬድኩት። አንድ ሰው የሰብዕዊ መብት ተሟጋች መሆኑ በተለይ በሉላዊ ዓለም ለመስራት መታደሉ የተለዬ ጸጋ ነው ያን ወደ ኢትዮጵያ ኢንቤስት ለማድረግ መታሰቡ ራሱ እንኳንስ እርምጃው ፍትሃት ነበር

ቅዱስ ሚኬኤል በዓመቱ እዮርን አስፈረደ! ተመስገን!

ምስል
 እንኳን ደህና መጡልኝ።  አስተረዬ ገላገለን! ቅዱስ ሚኬኤል በተደበበደበ በአመቱ እንሆ እዮርን አስፈረደ። ተመስገን! „እንደ በጎች ወደ ሲኦል የሚሄዱናቸው። እረኛቸውም ሞት ነው። ቅኖችም በማለዳ ይገዟቸዋል። ውበታቸውም ከመኖሪያቸው ተለይታ በሲኦል ታረጃለች።“  መዝሙር ፵፰ ቁጥር ፲፬ ከሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 23.01.2019 ከእመ ዝምታ። ህወሃት ስንት ድንኳን ጥሎ ይሆን? እንኳን ደስ አለሽ አላዛሯ ኢትዮጵያ!  እንኳን ደስ አለህ አማራ! እንኳን ደስ አለህ የጎንደር ህዝብ!  ጸሎት እዮርን አንኳኩቶ እንዲህ አሰበለ። ዛሬ ነው የ አማራ ይህለውና ተጋድሎ ገድል የታዬበት የታምራቱ ቀን! ተመስገን! የቅማናት ሊሂቃንም ደምር ተቀጣጠሩ ትልቁ ጭንቅላታችሁ እንሆ አይሆኑ ሆነ። ተመሰገን! ቀጣዩ አንበላችሁ ከቶ ማን ይሆን?! ሳጅን በረከት ስምዖን እና ሳጅን ታደሰ ጥንቅሹ በቁጥጥር ሥር መዋላቸው እንሆ ተደመጠ። እንዴት ደስ ይላል። ትልቅ እረፍት ነው አንዱ የሴራ ቸረቻራ እንሆ ተሰበረ። እንኩት አለ። የሴራው ጭንቅላት ተናደ። ተመስገን። ገንዘቡ አይደለም የነፍሰ ገዳይ ማህበር እንዲህ ዘመን ይፈርደዋል። የዛሬን ቅጽበት መራድም ይበቃል ...  https://www.youtube.com/watch?v=JLtV5USFX50 የ አቶ በረከት ስምኦንና አቶ ታደሰ ካሳ ጉዳይ በክልሉ ፍ / ቤት የሚታይ ነው - የአማራ ክልል ፀረ ሙስና ኮሚሽን https://www.youtube.com/watch?v=-jq9gPCwi18 ሰበር ዜና : በበረከት ስምኦን መያዝ የአዲስ አበባ ህዝብ ግልብጥ ብሎ አደባባይ በደስታ ወጣ :: እኛም ወጥተን እ