ለበደል ፕሮፖጋንዲስት አያስፈልገውም። ለበደልም የፖለቲካ ተንታኝ አያስፈልገው። በደሉን የሚመክት እራሱን በዲስፕሊን ያረቀ ተቋም እንጂ።
ለበደል ፕሮፖጋንዲስት አያስፈልገውም። ለበደልም የፖለቲካ ተንታኝ አያስፈልገው። በደሉን የሚመክት እራሱን በዲስፕሊን ያረቀ ተቋም እንጂ። የአማራን ሕዝብ በነፍስ ወከፍ በሩ ድረስ ሄዶ ቤቱን መቃብር ሲሆን፣ ጓሮው የራሱ አካል ሙት መንፈስ እና ሽታ ሲጎፈንነው፣ ቤተ እምነቶቹ ሲደፋሩ፣ ልጆቹ በፊቱ በማገጡ ሰብዕናወች እዬተሰደቡ ሲደፈሩ ………፣ ማሳው ሲነድ፣ የጤና ተቋሙ አመድ ሲሆን፣ የትምህርት ዓውዱ ሲወድም፣ አገልግሎት መስጫ ተቋማቱ በግፍ ወደ አመድነት ሲቀዬሩ፣ ተሰልፎ ሲረሸን፣ በአንድ ጉድጓድ በግሪደር በተቆፈረ ጉድጓድ ካለ ሃግ ባይ ሲያሸልብ፣ አትወልድም፣ አትከብድም ተብሎ ጽንስ ወጥቶ መላገጫ ሲሆን፣ ሰግቶ የሸሸውም አስፓልት አቆሸሽክ ተብሎ ሲንገላታ፣ ስብሰባ ተጠርቶ ሲረሸን፣ ሲታረድ፣ ጭካኔው፣ አረማዊነት አገር ምድሩን ሲያካልለው ዬፖለቲካ ሳይንቲስት፣ የማይክ ኤክስፐርት አያስፈልገውም። ችግሩ እራሱ ካሪክለም፣ ችግሩ እራሱ መፀሐፋ ነው። ምፅዓት የፊደል ገበታው የሆነ ህዝብ ቢኖር አማራ ብቻ ነው። ቀለጤው ፖለቲከኛ ዬአማራ ሕዝብ አልተበደለም ይላል። እንደ ሽንብራ ቂጣ እዬተገላበጠ ዬእሱ ወገን ካልተሰቃዬ ለእሱ የድሎት ዕለቱ ነውና። ዬሆኖ ሆኖ ግፍ በቃ ብለው ብቅ ዬሚሉትም በመደዳ ሲረሸኑ፣ ሲታገቱ፣ ሲታሰሩ፣ ሲሰወሩ፣ ሲፈረጁ ያያል፣ ይሰማል፣ ይኖርበታል ጭምቱ፣ ቅኑ ደጉ አማራ። ይህን ሁሉ ግፍ ችሎ ደግሞ የሁሉም ጎደሎ ማሟያ አቅሙ፣ ፖለቲካው፣ ሥነ - ልቦናው፣ ትውፊት ትሩፋቱ ይሆናል። ዬሰጠው፣ የቻለ ህዝብ የማይቻለውን ችሎ፣ የጭካኔ ሪሰርች እዬተሰራበት፣ እንደ ጥንቸል ቤተ ሙከራ ሆኖ ይወገዛል፣ ይረገማል። አንድም ቀን ስለ እሱ ደፍረው ለመመስከር፣ በስቃዩ በመከራው ሁሉ ያልኖሩ፣ ያልነበሩ ደግሞ ማት ያወርዱበታል። ዬሚገርመው እዬተጫኑት መንበርህ ልሁንም