ልጥፎች

ከዶር ለገሰ ቱሉ ዘለፋ፤ የአቀራረብ ዝበት፤ የኃላፊነት ዝንፈት፥ ዬችሎታ ኩስመት ፥ የሰብዕና ክሳት ሌላው ከዚህ ...

ምስል

SAVE LALIBELA .

ምስል
 

"እሱበእሱ ድርድር ለክፋ ቀን የተቀመጠው የጫካው ኦነግ የኢትዮጵያመሪ ሆኖ ሊመጣ? አይሰማ ጉድ የለም ።

ምስል
  እሱበእሱ ድርድር ለክፋ ቀን የተቀመጠው የጫካው ኦነግ የኢትዮጵያመሪ ሆኖ ሊመጣ? አይሰማ ጉድ የለም ። "የመከራን ቀን ዝም ብዬእጠብቃለሁ።" (ትንቢተ ዕንባቆም ምዕራፍም፫ ቁ ፲፯) አንድ አብይዝም ከራሱ ጋር ሽብሩን ይደራደራል። "ከንቱ የከንቱ ከንቱ።" ጠቅላይ ሚር አብይአህመድ በርከትከት ያሉ ሥውር ታጣቂወች፤ አፋኞች አላቸው። አዲስ አበባም አፓርታማ አላቸው ይህን መሰል ጉዳይ የሚያስፈፅሙበት። #ህገ ወጡ 1) ቄሮ ለማፍያ ተግባር የተመረጡትን ብቻ ይመለከታል። 2) ፎሌ 3) አባቶርቤ 4) "ሸኔ" የጫካው የኦነግ ክንፍ በሙሉ መረጃ እና ሎጅስቲክ ኢትዮጵያን ዘነዘናዋን ያስቀረው። ይህ ህገ ወጡ አደረጃጀት ነው። #ህጋዊው 1) ልዩ ኮማንዶ 2) ሪፓብሊካን ጋር ከአሜሪካ የተወረሰ፤ 3) ልዩ ኮማንዶ ከራሺያ የተቀሰመ ይመስለኛል፥ 4) ኢሊት ሠራዊት ከእስራኤል በቀጥታ የተቀዳ፤ የተኮረጄ፦ 5) የኦሮምያልዩ ኃይል፤ አሁን አሁን ደግሞ ከአማራ ፋኖ መግነን ጋር የኦሮምያ ሚሊሻም አይቅርብን ብለዋል፦ ቅናቱም ያብተከትካቸዋል። 6) መደበኛው ዬኢትዮጵያ የፖሊስ ኃይል የቀደመው ባህር፤ ምድር እና አዬር ኃይል አላቸው። 7) በደህንነቱ ዘርፍ ኢንሳን ጨምሮ በሲቢሉ፤ በወታደራዊው በሙሉ አቅሙ አለ። የህገ ወጡም፤ የህጋዊውም ጠቅላይ አዛዡ ሌኮ/ አብይ አህመድ ናቸው። ሁሉንም አቅደው ለተፈለገው የሽብር ተግባር ያሰማራሉ። የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ትናንት የተፈጠረችው ደቡብ ሱዳን ሳትቀር ክንድ እንለካካ እያለች ነው። በባዕታችን ወረዳም ሰይማለች።ስሜን ሱዳንም ጦርነቱ ገታት እንጂ አና ብላ ገብታ ለም መሬታችን አፈራጣ ይዛለች። እንዲያውም ሱዳን እርስበርስ ጦርነት ባይኖርባት ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ ቅጣቱን በጎንደር በኩል ያንዶለ

#መንግሥታዊ #አናርኪዝም።

ምስል
#መንግሥታዊ #አናርኪዝም ። "ከንቱ የከንቱ ከንቱ ሁሉም ነገር ከንቱ።"   የጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ መተንፈሻ ቧን ከኦሮሞ ሊቃናት ውጪ አይታሰብም። ፈፅሞ። ከሰሞኑም አንድ የኦሮሞ ሊቅ የጽህፈት ኃላፊ አድርገው ሹመዋል። ማንን ፈርተው። ሃግ የሚል የለም።እራስ እግሩ እሱበእሱ። የ የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ዶር ሙላቱ ተሾመ በምንም አግባብ እና በምን ውክልና እንደሆን አይታወቅም በዬቦታው ተኮፈውሰው አያለሁኝ። የኢትዮጵያን መንግሥት ወክለው በሁሉም መስክ አራጊ ፈጣሪ ናቸው። በዘመነ ህወሃት ስለመኖራቸው ቱክም ሹክም ሳይሉ የኖሩት ዶር ሙላቱ ተሾመ በተመሰጠረ ሥልጣን አክቲብሊ እዬተሳተፋ ነው። ማን ተፈርቶ? ማንስ አለና። ሞቅ ሞቅ ሲላቸው ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ ለሚያለዙት፤ ለሚያደነዙዙት ተከታዮቻቸው " #ኦሮሞ እና አማራ ቁጥሩን ለውጊያ ያውለው" እያሉ ያባጭላሉ። እሳቸው እራስ እግሩን የራሳቸውን ወገኖች ሃብት ማማ፤ ፖለቲካ ማማ፤ አህጉራዊ እና ሉላዊ ዕውቅና መንበር ላይ አስቀምጠው። የማይቀረው ነገር ግን ይህ ዘመናይነት ይቀደዳል። እሱ ባለው ዕለት። #ያለለት ። መኖሩም መትነኑም ያልተነገረለት ከ98% በላይ የሆነው የኦህዴድ ኦነግ ፓርላማ ይህን መሰል አናርኪዝም ጉዞ ፀጥ ረጭ ብሎ በዝምታ ሙሉ ድምፁን ይሰጣል። መብቱ ተጥሶ የፈለገ ነገር ተከውኖ አጽድቅ ሲባል በሁካታ እና በጥድፊያ #እያውካካ ያፀድቃል። "ነገርን ነገር ያነሳዋል" እንዲሉ ጋዜጠኞቻቸውን የሸኙት የኢትዮጵያ ህጋዊ ፕሬዚዳንት ወሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ ግን አሉ? ወይንስ ዶር ሙላቱ ናኙበት። ለመሆኑ ተመለሱ? ለነገሩ ምን አገባን እኛን። ለበይ ተመልካችነት እንኳን ያልተፈቀደልን ዘመናይነታቸውን እንኳን ማዬትም መብት አይደለም ተብሎ ሠርክ በድ

እኔ ሥርጉተ ሥላሴ ከአናርኪዝምሥርዓት የሚጠበቅየሽግግር የፍትህሥርዓት ዬለም።

ምስል
  እኔ ሥርጉተ ሥላሴ ከአናርኪዝምሥርዓት የሚጠበቅየሽግግር የፍትህሥርዓት ዬለም። "በውኑ እግዚአብሄር በወንዞች ላይ ተቆጥቷልን?" "ቁጣህ በወንዞች ላይ መዓትህም በባህር ላይ ነውን?" (ዕንባቆም፫ ቁ ፰)     ህግ ተፈፃሚነቱ ህግ ከሚያውቅ አካል ነው። ህግ ተከባሪነቱም ህግን ከሚያውቅ አካል ብቻ ነው። ኢትዮጵያ ህግ ናት ሥል ተፈጥሯዋን እንጂ በትውስት ርዕዮት የሚዳክረውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ማለቴም አይደለም።    የኦነግ መሠረቱም፤ ድልዳሉም፤ ሂደቱም ዘሃ ግራውም #አናርኪዝም ነው። ይህ ማህበረ አናርኪዝም በእኛ ሰው አማኝነት ዕድሉን ሰጥተን እንሆ በፍርስራሻችን ላይ ሃዘን ላይ እንገኛለን። ይህ ቢቀር ይህ ይሻላል የማይባለው በዴሞግራፊ ፋሺዝምን በኢትዮጵያ እዬተረጎመ የሚገኘው ኦነግ መራሹ ሥርዓት ህግም፤ ተፈጥሮም፤ ኤቲክስም ሞራልም ያዩኛል ብሎ የማያስብ ዝልኝ መንፈስ ነው። ከተፈጥሯዊነት ውጪም ነው። በጭካኔ እና በጥላቻ በማን አንሼ መንፈስ ነው የተፈጠረው። ካለ ጭካኔ መሽቶ አይነጋለትም። ሥርዓት ተለወጠ ሲባል ጃኬቱን እዬቀያዬረ ተስፋ ተቀቀለ።    ኦነግ መነሻውም መድረሻውም ጭካኔ እና አረመኔነት፤ ጥላቻ እና የሰውን ልጅ ከክብሩ ዝቅ አድርጎ የሚጨፈላለቅ ማት ነው። በእያንዳንዱ ቀን ከመርዶ ዜና በስተቀር ያልተተረፈበት የሥልጣን ዘመን በወንጀልም የዘለበ ነው። የተቋማት መኖር ብቻውን የሚፈይደው የለም። "የአሳ ግማቱ ከጭንቅላቱ" እንዲሉ ከዚህ ሥልጣን ላይ ካለው ስብስብ የስኳር ቆቆር ታክል ፍትህ አይጠበቅም።   ጊዜም፤ ወረትም መንፈስም ሊባክን ፈጽሞ አይገባም። ቁርጥ ያጥጋባል ይላሉ ባለ ቅኔወች ጎንደሮች ሲተርቱ። እንቁረጥ። እግዚአብሄር ሊያደርግልን እንደሚችል እናምናለን። ፍትህ ግን ከፋሺዝም ሊታሰብ ፈፅሞ አይ

Ethiopia clashes raise fears for historic churches

ምስል

ዋናውን ሚስጥር ነገሩኝ!#spiritual #rural #areassacred #songs #spiritualgrowth ...

ምስል

ዬነገረ ዶር ለገሠ ቱሉ መንገድ ሌሎቻችሁ ትማሩበት ዘንድ ነውና አትበሳጩ። #ፋኖ ለአማራ ህዝብ ቀይ የደም ሴላችን ነው። ይህ ዛሬ የተፃፈ አይደለም የታገልኩበት መሥመሬ ነው። ዛሬ ጄኒራሉ በርከትከት ሲል ከፍሬ መልስ በጎደለ ላይ ማተኮር የስንዱዋ ሥርጉትሻ አነባቢ መንገዷ ነው።

ምስል
ዬነገረ ዶር ለገሠ ቱሉ መንገድ ሌሎቻችሁ ትማሩበት ዘንድ ነውና አትበሳጩ። #ፋኖ ለአማራ ህዝብ ቀይ የደም ሴላችን ነው። ይህ ዛሬ የተፃፈ አይደለም የታገልኩበት መሥመሬ ነው። ዛሬ ጄኒራሉ በርከትከት ሲል ከፍሬ መልስ በጎደለ ላይ ማተኮር የስንዱዋ ሥርጉትሻ አነባቢ መንገዷ ነው።      "አቤቱ ታድነኝ ዘንድ ፍቀድ፤ አቤቱ እኔን ለመርዳት ፍጠን።" (መዝሙር ፴፱ ቁ ፲፫)     #ዕፍታ ። ዬሰሞንን የዶር ለገሰ ቱሉን ንግግር አደብ ገዝቼ አዳመጥኩት። የመልስ መልስ ለመስጠት አይደለም ቁም ነገሩ። ተያያዥ ጉዳዮች ወፍ ካወጣቸው ላነሳቸው እችላለሁኝ።   በኽረ ጉዳዬ የ፬ ኪሎ መንበር የምታልሙ፤ ይህም ባይሆን በተለያዬ ምክንያታዊ ገጠመኝ ህዝብ እናነቃለን፤ ባለፈም ህዝብ እንመራለን፤ እንዲያም ሲል ኮኦርድኔተር ነን፤ እንዲሁም አቅጣጫ ነዳፊ ነን የምትሉ ሁሉ ምን ተማራችሁበት ከዚህ መሰል ወጣ ገባ፤ ጠራጠሮ ሰብዕና፤ ከዚህ መሰል የኃላፊነት ቦታ ካለ የኢትዮጵያን አንደበት ከወከለ ሰው????   በመሪነት ላጫችሁ ይሁን ለታጫችሁ ሁሉ በዶር ለገሰ ቱሉ ቦታ እራሳችሁን አስቀምጡ እና እኔ ብሆን ብላችሁ እራሳችሁን እስኪ መዝኑት። እኔን አይመለከትም። ከዬትኛውም ተቋም ይሁን ተጽዕኖ ፈጣሪ ጋር ግንኙነት ዬለለኝ፦ በመቆጠብ እና እራስን በመግዛት ለራሴ ጥሪ፤ ለተፈጠርኩበት መልዕክት የምታትር ባተሌ ነኝ እና። ዕውቅናው #አይገጠግጠኝም ። #ውዳሴውም #አያሻቅለኝም ። ለዬትኛው የኃላፊነት ቦታም እራሴን አጭቼም አስቀምጬም አላውቅምና። #ሂደት እና ግጥምጥሞሹ። ዶር ለገሰ ቱሉን እያዳመጥኩኝ አሁን መድረክ ላይ፤ ሚዲያ ላይ ያሉትን ወገኖቼን ሁሉ በዕዝለ ህሊናዬ ሳስስ ነበር። ምክንያቱም የዚህ መከረኛ ባለቤት አልቦሽ ትውልድ ሮል ሞዴል ምንጩ፤ አቅጣጫው ውሉ ስለሚጠፋኝ።  

ሰማዕታት!!! የምስራቅ ፋኖ! 07.11.2022

ምስል
  ሰማዕታት!!! የምስራቅ ፋኖ! ይህ ሁሉ መገበር እና ትርፋን? የጀግኖች ውሎ እና ቀሪ የቤተሰብ ተስፋ???? ምን እና ምን፣ እንዴት እና እዴት ይሆን፣ ይኳኋን ይሆን?????? ፦፦፦፦፦ ይህ በጀግና መሬ ወዳጆ የሚመራው ብቻ ነው ሊስቱ። ከነሃሴ 18/2014 አስቸጋሪ ቦታወችን ጥሰው በመግባት በሦስት ቀን ብቻ 45 ባለፋት ሁለት ወራት ብቻ ከ75 አባላት በላይ ሰማዕትነትን ሲቀበሉ፣ የቆሰሉ፣ የአካል ጉዳት የደረሰባቸውም አሉ። ይህ የምስራቅ ፋኖ ብቻ እንጂ በጠቅላላ በዬጎበዝ አለቃው፣ በከፍተኛ መሪወች የሚመራውን አይጨምርም። የሆነ ሆኖ ሁለት ዓመት ሙሉ ሁለመናውን፣ መኖሩን የገበረ ቀጣይ ተስፋስ?????  

Die schreckliche Dunkelheit in der Stadt Nekmet in der Wolga Ormiay Region. 07.11.2022

ምስል
  • Die schreckliche Dunkelheit in der Stadt Nekmet in der Wolga Ormiay Region. #Mein Vorwort ist mit tiefer Traurigkeit...   Keine ausländische Regierung konnte den Sorgen der Amhara-Mütter Tränen standhalten. aber wieso? Manchmal fehlen einem die Worte, um seine Trauer auszudrücken. Ich habe heute Nacht nicht geschlafen. Ich habe die Fähigkeit verloren, meine Trauer zu schreiben. • Amahar Genozide ist weiter … und weiter …. Die ununterbrochenen Genozide der Amhara geht in Oromiay weiter. Eine Amhara-Mutter wurde in ihrem Haus mit ihren sechs Kindern in der Arsi-Zone in Jegue (Menbere - Hiyote Keblia oder Gemeinde) getötet. Weitere 9 Amhara-Eingeborene wurden brutal getötet. Vor einigen Tagen wurden 5 Amaras Stamm in einem benachbarten Ort in Addis Hiwet Gemeinde getötet. Inzwischen wurden in der Region Welga Tole Gemeint erneut Tausende Menschen getötet und weiter wieder 300 Amara-Leute vertrieben. (Der Bericht stammt von Heber Radio.) • Die schreckliche Dunkelheit in der

ዬአማራ እናት ከስድስት ልጆቿ ጋር ተገደለች። 07/11/2022

ምስል
  ዬአማራ እናት ከስድስት ልጆቿ ጋር ተገደለች።     ዬአሪሲዋ ሁሩርታም አዬሯ በስጋት እዬተናጠች ነው። "የቤትህ ቅናት በላኝ።" እያዘንኩ ነው እምጽፈው። በጢቾ ሮቤ መስመር ሌሊቱን ሁሉ ስትሄዱ ብታድሩ ምንም ንክች የሚያደርጋችሁ የደረቅ ወንጀል ፈፃሚ እንኳን አልነበረም። አይደለም የአማፂ ድርጅት አባላት። አሁን ግን የበዛ ስጋት ሙሉ አርሲ አንዣቧል። ከተሞች ለጊዜው ሰላም ቢመስሉም የገጠር ቀበሌወች ግን ኦነጋውያን በዛው በመከረኛው አማራ ላይ ጥቃታቸውን ቀጥለዋል። አንዲት እናት ከስድስት ልጆች ጋር፣ 9 አማራውያን ከሦስት ቀን በፊት ተመሳሳይ 5 ዬአማራውያን የንፁኃን ግድያ በገበሬ መንደሮች እዬተከወነ ነው። በአርሲ ጀጁ ……በመንበረ ሕይወት፣ በአዲስ ህይወት መንደሮች። ከገጠር ጀምረው ነው የዘር ማጽዳት ዘመቻው የተወጠነው። የዘመኑ የፖለቲካ ባህሬ ተረኝነት ሲባል አይደለም ይህ እጭ ላይ ያለ የፖለቲካ ዕሳቤ ነው። አሉታዊ ዴሞግራፊ ላይ ተቀምጦ ይህ መሰል የፖለቲካ ትንታኔ አዘናጊ፣ ትጥቅ አስፈቺ፣ አልዛዢ ነው። ዘመኑ የገዳ ወረራ፣ የገዳ፣ መስፋፋት፣ የገዳ አስምሌሽን፣ የገዳ ዲስክርምኔሽን ነው በማለት አዲስ አበባን ናሙና አድርጌ አራት ዓመት ሙሉ፣ ጽፌያለሁ ተናግሬያለሁ። የችግር መፍቻ አቅም የምታመነጨው፣ የችግሩን ዕውነተኛ ፍላጎት ስታውቀው ነው። በደራሽ እና በጭፍጫፊ አጀንዳ አቅም ሲባክን ባጁ። አሁን ነገረ አማራ ተራግፎ ሙት መሬት ላይ ይገኛል። አይነ ስውራን፣ አቅመ ደካሞች፣ አረጋውያን፣ ሴቶች፣ ህፃናት ካለምንም ሃግ ባይ ሰፊ ጥቃት እዬተፈፀመባቸው ይገኛል። ለዚህም ነበር አበክሬ በተከታታይ 1) ዓለም ዓቀፍ ጠበቃ ቀጥረን መጤም፣ ሰፋሪም ከተሆነ ህግ ይበይንብን። ሪፈረንስ የኔታ ፕ/ ዶር ሃብታሙ ተገኜ፣ ዬኔታ አቻምዬለህ ታምሩ የሠሩት ጥናታዊ

#የአብሽ ቡና።

  ዕለተ ሰንበት እናትነት በቅንነት ለውስጥነት። #የአብሽ ቡና። ስለአብሽ የጀምርኩት ነበር። ዛሬ ይከወናል። ግን እንደምን አደራችሁ? ደህና ናችሁን? #አብሽ እና ቡና። አብሽን ጭልጋ ገበሬ መንደር እንደቡና ሲጠቀሙበት አይቻለሁኝ። መንደሩን አልጠቅሰውም። ቡናው እዬተቆላ አብሹ ተጨመረ። ልኩን አይተው አወረዱት። ጠረኑ ስርንቅ ነበር። ተወገጠ። ተፈላ። እኔም ታደምኩበት። በጣም ይመራል። ብልኃት ይኖረዋል። የጤና ትሩፋት። እዚህ መጥቼ የተለያዩ አገር ቡናወች ጋር እዬቀላቀልኩ ጣዕሙን ለማምጣት ሞክሬያለሁኝ። ከአንድ ኮንብኔሽን ጋር ተመሳሳይ ሆኖ አግኝቼዋለሁኝ። ያው እንደነገርኳችሁ። ቤቴ ውስጥ በዚህ መሰል ጉዳይም አተኩራለሁ። እራሴን እንደ አንድ ኦብጀክት ወስጄ ማለት ነው። ገበሬው ቡናን በጥሬጨው፣ በጣዝማ፣ በማር ወይ በባዶ ይጠጣል። ጣዝማ ከማር ይገረምማል። ይከብዳል። ለጤናም ልዩ ነው። ጥሬጨው ማህል አገር ጨው እምትሉት ነው። ከእኛ ጨው አይባልም ጥሬጨው ነው። ትክክለኛ አማርኛ ትርጉሙም ይህ ነው። ሌላ የጨው ዓይነትም አለ። አሞሌ ጨው የሚባል። ለከብት የሚሰጥ። የሆነ ሆኖ የአብሽ ቡና ጠቀሜታውን ጠይቄ ባልረዳም ገበሬወች እንደሚጠቀሙበት አይቻለሁ። በስኳርም ሆኖ እጅግ በጣም ይመራል። ቤት ስመለስ ሞከርኩት ይመራል። በዚህ ይከወን። ደህና ሁኑ። መልካም ሰንበት። ቸር ወሬ ያሰማን አሜን። #ፎቶው ከአቶ ሰንጋ ተራ ፔጅ ያገኜሁት ነው። ሥርጉተ©ሥላሴ Sergute©Selassie 07/11/2021 ኑሩልኝ። አሜን።

07.11.2021#የአማራ ማዕልቱ አልተፀነሰም።

  #የአማራ ማዕልቱ አልተፀነሰም። ማዕልት ቀንና ሌሊት ማለት ነው። #ወጥ አማራ የተፎካካሪ ፓርቲ የቦርድ ሰብሳቢ፣ የድርጅት ማናጀር፣ ሚኒስተር፣ የበጎ ሰው ተሸላሚ ዓይናችሁ አይቷልን? ስለዘኔወማስሬ መልካም ዜና ከሐበሻ ዩኒቲ አዳምጫለሁ፣ አጭር መልዕክት ነው። አብይን ያመነ ጉም የዘገነ ነው። በዛ ስፈላሰፍ ነበር ያደርኩት። ተስማምተዋል ይላል ዘገባው። ከሆነ ጥሩ ነው። "በሬ ሆይ" እንዳይመጣ። አንድ እግር ዱር ቤቴ አንድ እግር ከተማ ይሁን አማራን መሪ አልባ ማስቀረት የግንቦትወአብይዝም ታላቁ የዘመኑ ፕሮጀክት ነው። የኢህአዲግ የግንባሩም ተፎካካሪ የሚባለውም ሊሂቁ የተነካ የለም ሲሾም ሲሸለም፣ የበጎ ሰው ሽልማት ሲሰጠው፣ የቦርድ አባል ሲሆን፣ ሚኒስተር ሲሆን ድርጅቱ ዕውቅና ሲሰጠው፣ በዶላር ሲደጎም፣ የዲፕሎማሲው ማህበረሰብ እንዲያውቀው መድረክ ሲመቻችለት አይተናል። አስተውለናል። ይህን ዕድል በርቁቅ መንገድ ያገኙትን አይተናል። የአማራ ሊሂቃን ሲሳደድ፣ ሲታሰር፣ ሲታገት ይህ ነው እንቅልፍ ነስቶኝ ያደረ። ለምን? አቶ ሽፈራው ሽጉጤ፣ አቶ ኃይለማርያም ደሴ ይንጎራደዳሉ? የቀደሙት የብአዴን ሹመኞች ከሥልጣን ገሸሽ ተደርገው አሉ እነ ገዳ ንጉሱ ጥላሁን እነ አቶ አዲሱ ወዘተ …… ዶር አንባቸው መኮነን የምስጥ ሲሳይ ሆኗል እስከ ቲሙ። ሁለት አባል ያለው የዶር አረጋይ በርሄ ፓርቲ በዕውቅና የአባይን ፕሮጀክት ይመራል። አቶ እስክንድር ነጋ ለ12 ጊዜ ከቲሙ ጋር ታስሮ ካልገደልነው ብለው በተራ ወንበዴ እዬተገለገሉ ነው ዶር አብይ አህመድ። 20 ዓመት ተደራጅቶ አዲስ ኃሳብ በማፍለቅ የማይታክተው፣ ግን በጠራራ ጠሐይ የሚዘረፈው የኢትዮጵያ ዕድል ፈር ቀያሽ የሆነው ኢዴፓ ዲስማንትል ሆኖ የዶር በዬነ ጴጥሮስ ፓርቲ ተሹሞ ድርጅቱ ቀጥሏል። ጫካ የነበረው