#መንግሥታዊ #አናርኪዝም።

"ከንቱ የከንቱ ከንቱ ሁሉም ነገር ከንቱ።"
 May be an image of 1 person
የጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ መተንፈሻ ቧን ከኦሮሞ ሊቃናት ውጪ አይታሰብም። ፈፅሞ። ከሰሞኑም አንድ የኦሮሞ ሊቅ የጽህፈት ኃላፊ አድርገው ሹመዋል። ማንን ፈርተው። ሃግ የሚል የለም።እራስ እግሩ እሱበእሱ። የ
የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዚዳንት ዶር ሙላቱ ተሾመ በምንም አግባብ እና በምን ውክልና እንደሆን አይታወቅም በዬቦታው ተኮፈውሰው አያለሁኝ። የኢትዮጵያን መንግሥት ወክለው በሁሉም መስክ አራጊ ፈጣሪ ናቸው። በዘመነ ህወሃት ስለመኖራቸው ቱክም ሹክም ሳይሉ የኖሩት ዶር ሙላቱ ተሾመ በተመሰጠረ ሥልጣን አክቲብሊ እዬተሳተፋ ነው። ማን ተፈርቶ? ማንስ አለና።
ሞቅ ሞቅ ሲላቸው ጠቅላይ ሚር አብይ አህመድ አሊ ለሚያለዙት፤ ለሚያደነዙዙት ተከታዮቻቸው "#ኦሮሞ እና አማራ ቁጥሩን ለውጊያ ያውለው" እያሉ ያባጭላሉ። እሳቸው እራስ እግሩን የራሳቸውን ወገኖች ሃብት ማማ፤ ፖለቲካ ማማ፤ አህጉራዊ እና ሉላዊ ዕውቅና መንበር ላይ አስቀምጠው። የማይቀረው ነገር ግን ይህ ዘመናይነት ይቀደዳል። እሱ ባለው ዕለት። #ያለለት
መኖሩም መትነኑም ያልተነገረለት ከ98% በላይ የሆነው የኦህዴድ ኦነግ ፓርላማ ይህን መሰል አናርኪዝም ጉዞ ፀጥ ረጭ ብሎ በዝምታ ሙሉ ድምፁን ይሰጣል። መብቱ ተጥሶ የፈለገ ነገር ተከውኖ አጽድቅ ሲባል በሁካታ እና በጥድፊያ #እያውካካ ያፀድቃል።
"ነገርን ነገር ያነሳዋል" እንዲሉ ጋዜጠኞቻቸውን የሸኙት የኢትዮጵያ ህጋዊ ፕሬዚዳንት ወሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ ግን አሉ? ወይንስ ዶር ሙላቱ ናኙበት። ለመሆኑ ተመለሱ? ለነገሩ ምን አገባን እኛን። ለበይ ተመልካችነት እንኳን ያልተፈቀደልን ዘመናይነታቸውን እንኳን ማዬትም መብት አይደለም ተብሎ ሠርክ በድሮን የሚጨፈጨፍ የአማራ ህዝብ ልጆች #አይደለምን?
በሌላ አገሮች ልምድ እንዲያካፍሉ በዩንቨርስቲወች፤ በፓናል ዲስከሽኖች አልፎ አልፎም በቃለ ምልልስ ጥሩታ ከተወጣ፤ ተፈቅዶ ሥልጣን ከተለቀቀ በኋላ ከሚገኜው በረከት በስተቀር እንዲህ የኢትዮጵያን መንግሥት ወክሎ በዲፕሎማሲው ዘርፍ በትጋት እና በተከታታይነት፤ በፀጥታ ዘርፍ መቧረቅ #ሥርዓተ #አልበኝነት ነው። ለነገሩ ኦነግ እና ሥርዓት እንዴት ተብሎ? "ያለአባቱ ዶሮ ባጓቱ።"
ይፋዊ ሥልጣን ከሰጠ ማህበረ ኦነግ ኢትዮጵያን ሃይጃክ ስለአደረገ ኦነግ ሥርዓትም ተፈጥሮውም ሥላልሆን በቀላጤ ቢገልጠው ይሻለው ነበር። እንዲህ የውሽማ ሞት ሆኖ ከሚትበሰበሱ።
የሚገርመኝ ለመብቱ የሚታገል አንድም የኦነግ ሊቅ አለመኖሩ ነው። እንደ ተገዛ በግ መጎተት ብቻ። ለኢትዮጵያም #ጭነት። ፈርዶባት። መጥኔ አንቺ አገር ኢትዮጵያ።
እግዚአብሄር ይስጥልኝ።
ግን እንዴት ናችሁልኝ?
ሥርጉተ©ሥላሴ
Sergute©Selassie
10/11/2023
ጊዜ ራዲዮሎጂ ነው።

 

አስተያየቶች

ከዚህ ጦማር ታዋቂ ልጥፎች

ዛሬ ያለው ነገር „ፈረቃም፤ ተረኝነትም“ አይደለም።

እህት አጊቱ ጉደታ አገር ነበረች።

አብይ ኬኛ መቅድም።